Site icon ETHIO12.COM

9+1= ስንት ነው? የማይጠብሪ ግንባር ሰሞነኛ የጨዋታ ውጤት

ህወሓታዊያን የሽብር አለቆች ስንት ያለሙበት የማይጠብሪ ግንባር ሰሞነኛ የጨዋታ ውጤት።

የጨዋታው አዝማቾች:-

ጦርነት ባህላዊ ጨዋታችን ነው! ያሉት ምግበይ መራሽ ከሃዲያውያን ።

የጨዋታው ተሰላፊዎች :-

የጁንታ መንጋ ክ/ጦሮች (9+1)
የቅማንት ቅጥረኛ ቡድኖች መንገድ መሪ
የኦነግ ሸኔ አባላት
ከሱዳን የተመለመሉ ስደተኞች

የጨዋታ ጀማሪዎች ዋና አላማ፦

በዳባትና ደባርቅ መካከል ቆርጦ በመግባት ወደ ጎንደር በመገስገስና የሁመራ ኮሪደርን በማስከፈት ከእኩይ አላማ ከተጋሪዎቻቸው ጋር በመገናኘት ለማንኛውም የውጭ ሀይሎች ድጋፍና እርዳታ ምቹ ሁኔታ መፍጠር ።
– የአማራ ህዝብን መግደል ፣ መዝረፍ
– ለውጭ ሀይሎች በር መክፈት

የጨዋታው ጅማሮ:-
ያለፈው ሳምንት

የጨዋታው አውዶች:-

በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅና ዳባት ወረዳዎች ውቅን ጭና እና ጫንቅ።

የጨዋታው ውጤት:-

ኢትዬጵያውያንን አንገት ለማስደፋት ያለ የሌለ ሀይሉን ተጠቅሞ በከሃዲው ጄኔራል ምግበይ ሀይለ ቁንጮነት በአርሚ-1 አደረጃጀት በ3 ኮሮች የተደራጀው 9 እግረኛ ክ/ጦር እና የኮማንዶ ሻለቆች አሰልፎ በማይጠብሪ ግንባር ወረራ የከፈተው የጁንታ ሀይል ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል ሲሉ ለህዝባችን የድል ዜና ያሰሙት ሜ/ጄ መሰለ መሰረት የምዕራብ ዕዝ እና የማይጠብሪ ግንባር አዛዥ ናቸው።

እናም አሉ ጄኔራሉ ! “ምንግዜም ያለውን ሁሉ ሰጥቶ ደጀን የሆነንን ህዝብ ይዘን የማንወጣው ተራራ የማንደመስሰው ጠላት የለም”።

አሁን ላይ:-

በምዕራብ ዕዝ ትንታጎች መሪነት የአማራ ልዩሀይል ፣ ሚሊሻና ፋኖ እንዲሁም የኦሮሚያ ሚሊሻ አባላት የጁንታውን የመጨረሻ ቀብር በአዲስ አመት ለማብሰር ለቀጣይ ግዳጅ በመጠባበቅ ላይ ናቸው።

የምስጋና ገፅ:-
ደጀን ለሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ
ለሰሜን ጎንደር ህዝብ
ለፅኑዎች የደባርቅና ዳባት ወጣቶች

የሚገርመው ግን !

ማይጠብሪ ግንባር የተሰለፈው የወገን ክንድ ፣ ከአካባቢው ተፈጥሯዊ መልክዓ ምድርና እንደ አሸን ፈልተው በሰረጉ 9+1 የጁንታ ክፍለጦሮች ፣ የቅማንት አክራሪ ፣ የኦነግ ሸኔ እና የሱዳን ስደተኛ ጀሌዎች በደባርቅና ዳባት ተራሮች “እምሽክ” አድርጓቸዋል።

መቼም “ኢትዮጵያ ታሸንፋለች”

መላክ በቃሉ (ከግዳጅ ቀጣና)
ፎቶግራፍ ተሰማ ኡርጌሳ

ENDF Facebook

Exit mobile version