Site icon ETHIO12.COM

ዘጠነኛው የበጎ ሰው ሽልማት ተካሄደ

(ይትባረክ ዋለልኝ)

የ2013 ዓ.ም “ ዘጠነኛው የበጎ ሰው ሽልማት” ዛሬ እሑድ ነሐሴ 30 ቀን 2013 ዓ.ም በኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል አዳራሽ ተካሂዶ ነበር።በክብር እንግድነት የተገኙት የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ ነበሩ::በዚህ ለዘጠነኛ ጊዜ በተዘጋጀው የ 2013 ዓ.ም የበጎ ሰው የሽልማት ፕሮግራም ላይ በ አስር ዘርፎች ሽልማት ተሰጥቷል:: በዚህም መሰረት በሁሉም ዘርፍ እጩ ሆነው የቀረቡትንና ተሸላሚዎቹ እንደሚከተለው ቀርበዋል::

1. በኪነጥበብ ዘርፍ እጬዎች የነበሩት

_ በዕውቀቱ ስዩም

_ ጃርሶ ሞትባይኖር ኪሩቤል

በዚህ ዘርፍ ከእነዚህ እጩዎች መካከል የ2013 ዓ .ም የበጎ ሰው ተሸላሚ የሆኑት

በዕውቀቱ ስዩም ነው:: የበእውቀቱ ስዩምን ሽልማት የተቀበሉት አባቱ አቶ ስዩም መሰለ ናቸው::

2.በማህበራዊ ጥናት ዘርፍ እጬዎች የነበሩት

_ ፕሮፌሰር ጥላሁን ተሾመ

_ ፕሮፌሰር ጌትነት ታደለ

_ ፕሮፌሰር አሉላ ፖንክረስት

በዚህ ዘርፍ ከእነዚህ እጩዎች መካከል የ2013 ዓ .ም የበጎ ሰው ተሸላሚ የሆኑት

ፕሮፌሰር ጥላሁን ተሾመ ናቸው::

3 . በቅርስና ባሕል ዘርፍ እጬዎች የነበሩት

_ ዶ/ር መንግስቱ ጎበዜ

_ አቶ ሲሳይ ደምሴ

_ ቢላል ሐበሽ ሙዚየም የልማትና የበጎ አድራጎት ማህበር ሲሆኑ

በዚህ ዘርፍ ከእነዚህ እጩዎች መካከል የ2013 ዓ .ም የበጎ ሰው ተሸላሚ የሆኑት

ቢላል ሐበሽ ሙዚየም ናቸው::

4.በመምህርነት ዘርፍ እጬዎች የነበሩት

– ዶ/ር ልዑል ሰገድ አለማየሁ

– ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ

– ፕሮፌሰር ጥሩሰው ተፈራ ሲሆኑ

በዚህ ዘርፍ ከእነዚህ እጩዎች መካከል የ2013 ዓ .ም የበጎ ሰው ተሸላሚ የሆኑት

ዶ/ር ልዑልሰገድ አለማየሁ ናቸው::

5.በሚዲያና በጋዜጠኝነት እጬዎች የነበሩት

_ ጋዜጠኛ ደጀኔ ጥላሁን

_ ዶ/ር ንጉሴ ተፈራ

_ ስለአባት ማናዬ

በዚህ ዘርፍ ከእነዚህ እጩዎች መካከል የ2013 ዓ .ም የበጎ ሰው ተሸላሚ የሆኑት

ዶ/ር ንጉሴ ተፈራ ናቸው::

6. በበጎ አድራጎት እጬዎች የነበሩት

– ማርያም ሙኒር

– እልልታ ውመን አት ሪስክ ግብረሰናይ ድርጅት

– አቶ አማረ አስፋው ሲሆኑ

በዚህ ዘርፍ ከእነዚህ እጩዎች መካከል የ2013 ዓ .ም የበጎ ሰው ተሸላሚ የሆኑት

አቶ አማረ አስፋው ናቸው::

7. በሳይንስ ዘርፍ እጬዎች የነበሩት

_ ዶ/ር አየለ ተሾመ

_ ኤመሬትስ ፕሮፌሰር አለማየሁ ተፈራ

_ ፕሮፌሰር የወይንሐረግ ፈለቀ ሲሆኑ

በዚህ ዘርፍ ከእነዚህ እጩዎች መካከል የ2013 ዓ .ም የበጎ ሰው ተሸላሚ

ኤመሬትስ ፕሮፌሰር አለማየሁ ተፈራ ናቸው::

8. በንግድና ሥራ ፈጠራ ዘርፍ እጬዎች የነበሩት

_ ወ/ሮ ብሩክታዊት ጥጋቡ

_ አቶ በላይነህ ክንዴ

_ ፓን አፍሪክ ግሎባል ኩባንያ

በዚህ ዘርፍ ከእነዚህ እጩዎች መካከል የ2013 ዓ .ም የበጎ ሰው ተሸላሚ የሆኑት

አቶ በላይነህ ክንዴ ናቸው::

9. መንግስታዊ የስራ ኃላፊነት በብቃት በመወጣት ዘርፍ እጬዎች የነበሩት

_ ኢንጂነር ሐብታሙ ተገኝ

_ ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ

_ አቶ ይኩኑዓምላክ መዝገቡ

በዚህ ዘርፍ ከእነዚህ እጩዎች መካከል የ2013 ዓ .ም የበጎ ሰው ተሸላሚ የሆኑት

ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ናቸው::

10.ኢትዬጵያ መልካም ስራ የሰሩ ዲያስፖራዎች ዘርፍ እጬዎች የነበሩት

_ ዶ/ር እንዳወቀች ዘርጋው

_ አለምፀሐይ ወዳጆ

_ ኤልያስ ወንድሙ

በዚህ ዘርፍ ከእነዚህ እጩዎች መካከል የ2013 ዓ .ም የበጎ ሰው ተሸላሚ የሆኑት

አቶ ኤልያስ ወንድሙ ናቸው::

የ2013 ዓ.ም የበጎ ሰው ልዩ ተሸላሚ የሆኑት

ጸሐፊ ትዕዛዝ አክሊሉ ሐብተወልድ ናቸው::

በዛሬ የ2013 ዓ.ም የበጎ ሰው ተሸላሚዎቹ ሽልማት የተሰጠ ሲሆን በየዘርፉ እጩ ሆነው ለቀረቡት የሰርተፍኬት ሽልማት ተሰጥቷቸዋል:: በዚህ የሽልማት ፕሮግራም ላይ መምህርና ተማሪ የሆኑት ሁለት ሰዎች ተሸልመዋል:: ተሸላሚው መምህር ኤመሬትስ ፕሮፌሰር አለማየሁ ተፈራ ሲሆኑ ተማሪው ተሸላሚ ደግሞ ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ናቸው:: ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በዛሬው እለት ከመምህሬ ጋር በመሸለሜ እጅግ ደስተኛ ነኝ ብለዋል::

Exit mobile version