ድንቁ ኢትዮጵያዊው ተመራማሪ ፕሮፌሰር ጋቢሳ ኢጄታ የአሜሪካን ብሄራዊ የሳይንስ ሜዳሊያ ሽልማትን ከፕሬዚደንት ጆ ባይደን መቀበላቸው ለአገር ኩራት፣ ለወገን ኩራት በመሆኑ የደስታ መልዕክት በርካታ ዜጎች በማህበራዊ ሚዲያ አጉርፈዋላቸዋል።
ሸዋ ኦሎንኮሚ የተወዱት ፕሮፌሰር ገቢሳ በዕጽዋት ዘረመል ማዳቀል እና ዓለም አቀፍ ግብርና ተመራማሪ፣ የፑርዱ ግሎባል የምግብ ዋስትና ማዕከል ዋና ዳይሬክተር፣ ሲሆኑ ሽልማቱንም ከአሜሪካ ብሔራዊ የሳይንስ ሜዳሊያን ከፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እጅ ተረክበዋል።
ፕሮፌሰር ጋቢሳ በፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ብሔራዊ የክብር ሽልማት ከተሸለሙ 21 አሜሪካውያን ተመራማሪዎች መካከል አንዱ ለመሆን የበቁ መሆናቸው በታሪካ ተመዝግቧል። የኢትዮጵያ መንግስትም በእኚሁ ድንቅ ኢትዮጵያዊ ታሪክና ተግባር አገር መክራቷን ጠቅሶ “እንኳን ደስ አለዎት” ሲል በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አማካይነት መግለጫ አውጥቷል።
መምህርና ተመራማሪው ፕሮፌሰር ጋቢሳ ኤጄታ ለሽልማቱ ያበቃቸው በከፍተኛ የምርምር ስራቸው የእፅዋት ዘረመል ምህንድስና በመጠቀም በረሃማ የአየር ንብረት እና ነፍሳትን የሚቋቋሙ የአዝርዕት ዘሮችን በማግኘታቸው ባገኙት የልህቂነት ክብር ሳቢያ ነው። ይህ ድንቅ ተብሎ ለታላቅ ሽላማት ያበቃቸው ግኝታቸው በሚሊዮን ለሚቆጠሩ የዓለም ፍጡራን የምግብ ዋስትናን እንደሚያረጋግጥ ያታመነበት ሆኗል።
ፕሮፌሰር ጋቢሳ ኤጄታ በምግብ ዘርፍ ላበረከቱት አስተዋፅዖ ከዚህ በፊት ከዓለም የምግብ ፕሮግራሙ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በተለያዩ መድረኮችም ከፍተኛ ክብር አጎናጽፏቸዋል።
ፕሬዚደንት ባይደን በይፋዊ የማህበራዊ ገጽ አውዳቸው እንዳሉት የተሸላሚዎች ዝርዝር በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ዘርፍ ለሽልማት የበቁትን ተመራማሪዎች እንኳን ደስ ያላችሁ በሚል አውድሰዋል። የኢትዮጵያ መንግስትም ሽልማቱ ይፋ መሆኑንን ተከትሎ የሚከተለውን ‘ የንኳን አደረሰዎ” መግለጫ አሰራጭቷል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአሜሪካን ብሄራዊ የሳይንስ ሜዳሊያ ሽልማትን ላገኙት ለፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጄታ የእንኳን ደስ ያለዎት መልዕክት አስተላልፏል።
ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጄታ የአሜሪካን ብሄራዊ የሳይንስ ሜዳሊያ ሽልማትን ከፕሬዝደንት ጆ ባይደን ተቀብለዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በእንኳን ደስ ያለዎት መልዕክቱ ሽልማቱ ፕሮፌሰሩ በዕጽዋት ዘረመል ማዳቀል ላይ ላበረከቱት አስተዋጽኦ መሆኑን ገልጿል።
ፕሮፌሰር ገቢሳ በዕጽዋት ዘረመል ማዳቀል እና ዓለም አቀፍ ግብርና ተመራማሪ፣ የፑርዱ ግሎባል የምግብ ዋስትና ማዕከል ዋና ዳይሬክተር፣ ሲሆኑ ሽልማቱንም ከአሜሪካ ብሔራዊ የሳይንስ ሜዳሊያን ከፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እጅ ተረክበዋል። ሽልማቱ አሜሪካ በተለያዩ ዘርፎች ለተሰማሩ ተመራማሪዎች የምትሰጠው ከፍተኛ እውቅና ነው።
ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጄታ በማሽላ እህል ላይ ሰፊ ጥናት ያደረጉ ሲሆን እ.አ.አ በ2009 የከፋ ድርቅ እና አጥፊ አረምን የሚቋቋሙ የማሽላ ዝርያ ላይ ባደረጉት ምርምር የዓለም ምግብ ሽልማትን አግኝተዋል ።
ይህ ምርምራቸው ከፍተኛ የማሽላ ምርትን በመጨመር ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመመገብ ረድቷል።
ፕሮፌሰር ገቢሳ በፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ብሔራዊ የክብር ሽልማት ከተሸለሙ 21 አሜሪካውያን ተመራማሪዎች መካከል አንዱ ሆነዋል። በዚህም መንግስት ክብር እንደተሰማው ገልጾ ደስታውን ገልጾላቸዋል።
- Ethiopia Working To Secure New Development Bank MembershipThe Ministry of Foreign Affairs disclosed that Ethiopia is working hard to become member of BRICS’ New Development Bank. In a media briefing regarding… Read more: Ethiopia Working To Secure New Development Bank Membership
- የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”በአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች መመስከራቸውን ቢቢሲ አስታወቀ። ይህ የተገለጸው ከአለማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ከሃምሳ ሺህ… Read more: የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”
- በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነውለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ መያዙንna ለዚህም ተግባራዊነት ከሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊየን በላይ ችግኝ መዘጋጀቱን ተገለጸ። 1 ነጥብ… Read more: በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነው
- አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠአፍሪካ ህብረት የውጭ ምንዛሬ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር እንደሚያዘዋውር ተጠቅሶ በህብረቱ ስም የወጣው ዜና ሃሰት፣ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ መሆኑን መንግስት አስታወቀ። መረጃው ቀድሞውንም ዜናው… Read more: አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠ
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ። አሁን ምኑ ነው አፍሪካ ህብረትን ስጋት… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች