Site icon ETHIO12.COM

የኢትዮጵያ መንግስት 7 የተመድ ሰራተኞች በ72 ሰአታት ውስጥ ከአገር እንዲወጡ ትእዛዝ አስተላለፈ

የኢትዮጵያ መንግስት 7 የተመድ ሰራተኞች በ72 ሰአታት ውስጥ ከአገር እንዲወጡ ትእዛዝ አስተላለፈ


የኢትዮጵያ መንግሥት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ስር በተለያዩ ኤጀንሲዎች ውስጥ የሚሰሩ 7 የውጭ አገር ዜጎች በ72 ሰዓት ውስጥ ኢትዮጵያን ለቀው እንዲወጡ ትእዛዝ ማስተላለፉን የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኢቲቪ በላከው መረጃ እንዳስታወቀው የኢትዮጵያን ድንበር ለቀው እንዲወጡ የታዘዙት የመንግሥታቱ ድርጅት ባልደረቦች በአገር ውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ህገ ወጥ ሥራ ሲሠሩ የተገኙ መሆናቸውም ነው የተገለፀው።

የኢትዮጵያን ድንበር ለቀው እንዲወጡ የታዘዙት ሰባት የውጭ አገር ዜጎች

1- የዩኒሴፍ የኢትዮጵያ ተወካይ UNICEF ሚስ አዴል ኮደር

2- የዩኤን የተራድኦ ምክትል አስተባባሪ ግራንት ሊያቲ

3- የዩኤን የተራድኦ ምክትል አስተባባሪ ተወካይ ሚስ ጋዳ ኤልታሂር ሙዳዊ፣

4- የዩኤን የሰላምና ልማት አማካሪ ከውሲ ሳንቼሎቲ

5- የሰብአዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ቢሮ ባልደረባ ሶኒ ኦኒግ ቡላ

6- የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅ/ቤት UNOCHA ምክትል አስተባባሪ ሰኢድ መሀመድ ሀርሲ

7- የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅ/ቤት UNOCHA ኃላፊ ሚስ ማርሲ ቪጎዳ ናቸው።

Via – EBC

Exit mobile version