አሸባሪው ህወሃት በአማራ ክልል ሰሜን ወሎና በጎንደር የህዝቡን የኢኮኖሚ መሰረቶች አውድሟል
አሸባሪው ህወሃት በአማራ ክልል ሰሜን ወሎና በጎንደር የህዝቡን የኢኮኖሚ መሰረቶች ማውደሙን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ህዝቡን ለመከራና ስቃይ በመዳረግ ዳግም ወደ ፖለቲካ ስልጣን ለመምጣት አደገኛ ሙከራ ውስጥ የተዘፈቀው ላለፉት 27 አመታት ስልጣን ላይ የነበረው አሸባሪው ቡድን፤ አብዛኛው የትግራይ ክልል ህዝብን ከሴፍቲኔት ተረጅነት እንኳን ሊያላቅቅ አልቻለም፣ ቡድኑ ለክልሉ ህዝብም ደህንነት ያለውን ግዴለሽነት በተደጋጋሚ አሳይቷል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አሸባሪ ቡድኑ በወረራቸው የሰሜን ወሎና ጎንደር አካባቢዎች ያደረሰው መጠነ ሰፊ ውድመት የአማራ ህዝብ ጠላትነቱን ዳግም ያስመሰከረበት መሆኑን ገልጿል።
በወረራ ከያዛቸው አካባቢዎች የሚወጡ ሪፖርቶች እንዳመለከቱት የብዙ ቤተሰቦች የኢኮኖሚ አቅሞችን አውድሟል፤ በወረራቸው አካባቢዎች ያሉ አርሶ አደሮች የአሸባሪው ታጣቂዎች የደረሱ ሰብሎችን እየዘረፉ ማመልከታቸውን ጠቅሷል።
“አርሶአደሩ ያከማቸው እህል ተዘርፏል የቀረውም እንዲወድም ሆኗል፤ የእርዳታ እህል ማከማቻ መጋዘኖች የአሸባሪው ቡድን የዘርፋ ሰለባ ከመሆናቸው ባሻገር ከተረጂዎችም ይቀማል” ብሏል መግለጫው፡፡
ቡድኑ ያስከተለው መጠነ ሰፊ ውድመት በግለሰብ ላይ ብቻ ሳይሆን እንደማህበረሰብ የህዝብ መገልገያዎችን የህፃናት መዋያዎች፣ ትምህርት ቤቶች፣ ኮሌጆች፣ ባንኮች፣ የጤና ማዕከላት፣ ሆቴሎችና ሎሎችም ተቋማት ወድመዋል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን ለጎን የትግራይ ከፍተኛ ባለስልጣናትና የዞን አስተዳዳሪዎች የተባሉ ሁለት ዓይነት መረጃዎች እየሰጡ ነው። መንግስት ግን ስምምነት መኖሩን ዘርዝሮ እነሱ በሚሉት መልኩ ባለመሆኑ ” ትዕግስት ፍርሃቻ አይደለም” እያለ ነው።ከትናንት በስቲያ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ግንባታ ማስተባበሪያ እና… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች ዜና የሚያቀብሉና እነሱኑ የሚከተሉ ስምምነቱ መክሸፉንና መንግስት ውሉን እንደተወው፣ የሶማሌ ማንግስትም መንግስት በአደባባይ ስምምነቱን ማቆሙን እንዲያውጅ እንደሚያደርግ አስታውቀው እንደነበር ይታወሳል። ሌሎች አገራት ከሶማሌላንድ ጋር መሰል ስምምነትን ሲያደርጉ ዝምታን የመረጡ፣ የግብጽን፣ የኤርትራንና የሶማሌን የተቀነባበረ ሴራ ተከትለው ኢትዮጵያ… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን ዋስትና አፀና። ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎቹ ከሀገር እንዳይወጡ እግድ እንዲጣል ትዕዛዝ ሰጥቷል። ተጠርጣሪዎቹ የቀድሞ የህዝብ ትራንስፖርት የተሽከርካሪ ዘርፍ ኃላፊና የትራንስፖር ሎጂስቲክ ሚኒስትር አማካሪ የነበሩት ከድልማግስት ኢብራሂም፣ የትራንስፖርት ማህበራት አመራርና አባል ታምራት በየነ፣ ጌትነት በየነ እንዲሁም የመናኸሪያ የትራንስፖርት ስምሪት ኃላፊዎች… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት ውስጥ የሚኖሩ ዜጎቹን መልሶ ለመቀበል ያሳየው ተባባሪነት አናሳ መሆኑን ካውንስሉ ባደረገው ግምገማ ስለተገነዘበ” ነው። “የኢትዮጵያ ባለሥልጣኖች ዜጎችን መልሶ ለመውሰድ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ አልሰጡም” በማለት የካውንስሉ መግለጫው ያብራራል። የአስቸኳይ ጊዜ የጉዞ ሰነዶች በመስጠት እንዲሁም በፍቃድ እና ያለ ፈቃድም የሚደረግ… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
በግንባታ ሂደት ላይ ያለው የአዋሽ ወልዲያ ሃራ ገበያ የባቡር መንገድ ፕሮጀክት ሃላፊነት በማይሰማው አሸባሪ ቡድን የጥቃት ሰለባ ሆኗል ፡፡
“ሽብር ቡድኑ የሚያስከትላቸው መጠነ ሰፊ ውድመቶች ለትግራይ ህዝብ የሚፈይድለት ነገር እንደሌለ ይታወቃል፤ ይልቁንም የትግራይና የአማራን ህዝብ ወደ ባሰ ስቃይና እንግልት ያስገባል” ሲል ሚኒስቴሩ አመልክቷል፡፡
የሽብር ቡድኑ በሰሜን ወሎ እንዲሁም በጎንደር የፈፀመውና እየፈፀመ ያለው ውድመት በፖለቲካው አለሁ ለማለት የሚደረግ የመጨረሻው መፍጨርጨር እንደሆነም ነው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ያስታወቀው፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት የአለም አቀፉ ማህበረሰብ በችግር ውስጥያሉና እገዛ የሚሹ በሰሜን ወሎና ጎንደር ያሉ ህዝቦችን ትኩረት እንዲሰጣቸው የጠየቀው መግለጫው፤ ወራሪው በያዛቸው አካባቢዎች ያሉ ዜጎች የተፋጠነ የሰብአዊ እርዳታ እንዲደርሳቸው ጥሪ አቅርቧል።
Ena