Site icon ETHIO12.COM

22 የአሸባሪው ካዋርጃ አባላት ባሌ ውስጥ በቁጥጥር መዋላቸውን ፖሊስ አስታወቀ

መሣሪያ ታጥቀው በባሌ ደኖች ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 22 የአሸባሪው ካዋርጃ አባላት በፀጥታ ኃይሎች ጥምረት ባሌ ውስጥ በቁጥጥር መዋላቸውን የዞኑ ፖሊስ አስታወቀ።

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ የኦሮሚያ ፖሊስ እና ሚሊሺያ ባደረጉት የተቀናጀ ክትትል አንድ የውጭ ሀገር ዜጋን ጨምሮ የእስልምና ሃይማኖትን የሚሰብኩ በማስመሰል ለሽብር ድርጊት ሰዎችን ሲያሰለጥኑ እና ሎጂስቲክስ ሲያቀርቡ የነበሩ የቡድኑ አባላት ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ነው ፖሊስ የገለጸው።

የፀጥታ ኃይሎች እንደገለጹት የቡድኑ አባላት ወጣቶችን እና ተሰሚነት ያላቸውን ግለሰቦች በመምረጥ የሸሪአ ሕግ የሚያስተምሩ በማስመሰል ወታደራዊ ሳይንስ ሲያስተምሩ ነበር።

በተጨማሪም ትክክለኛው የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ እናንተ ብቻ ናችሁ በሚል ትርክት ሞልተው ሌሎች ሰዎችን እንዲጠሉ እና የአጥፍቶ ጠፊ ድርጊት እንዲፈፅሙ የሚያሰለጥኑ መሆኑም ተገልጿል።

በቁጥጥር ስር የዋለው የአሸባሪው ካዋርጃ ቡድን ለሦስት ወራት ፑንት ላንድ ውስጥ ወታደራዊ ሳይንስ የሰለጠኑ አባላትን ያካተተ መሆኑን ኦቢኤን ዘግቧል።

Exit mobile version