Site icon ETHIO12.COM

ነጭ ወያኔዎች

በአሳየናቸው ክፍሌ

ታኅሣሥ 5/2014 (ዋልታ) የአሸባሪው ሕወሓት መራሹ መንግሥት በሥልጣን ላይ በቆየባቸው ዓመታት ከኢትዮጵያ ሕዝበ በመዝረፍ 30 ቢሊዮን ዶላር በውጭ አገራት እንዳከማቸ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

የሽብር ቡድኑ የዘረፋውን ዶላር ለአንዳንድ የአሜሪካ ባለሥልጣናት በማገራት ለሥልጣን መጠበቂያው ሲጠቀምበት ነው የቆየው፡፡

እነዚህ የጥቅሙ ተጋሪ የሆኑ የአሜሪካ ባለሥልጣናት የሕወሓት ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ እስኪመስሉ ድረስ የሕወሓትን ጥቅም ለማስከበር በተለያዩ መድረኮች ለቡድኑ ሲሞግቱ ታዝበናል፡፡

አሸባሪው ሕወሓት ከቆመበት የገደል አፋፍ ላይ ወደ መቀመቅ ከመውረድ ያተርፈኛል ብሎ ብርቱ እምነት ያለውም በእነዚህ ነጮቹ ወያኔዎች ላይ ነው፡፡

ይህ መተማመን ግን እነድ እነደዋዛ የመጣ አደለም ሕወሓትን ከደደቢት በረሃ በአንቀልባ አዝለው ደወ ውቤ በረሃ ያስገቡ የአሜሪካ ሰዎች አሁንም በነጩ ቤተ መንግሥት ፈላጭ ቆራጭ ውሳኔ ሰጪ በመሆናቸው ነው፡፡

እነዚህ ሰዎች ደግሞ በወያኔ ፍቅር ጨርቃቸውን የጣሉት በግል ግንኙነት ካላቸው ወዳጅነት ብቻ አደለም፤ ይህ ወሮበላ ማፊያ ቡድን በሥልጣን ላይ በነበረበት ጊዜ ከኢትዮጵያ በመዝረፍ ካከማቸው 30 ቢሊዮን ዶላር ተቋዳሽ በመሆናቸው ነው፡፡

ጌል ስሚዝ፣ ሱዛን ራይዝ፣ ዌንዲ ሼርማ፣ ጄፍሪ ፊልትማን እና ሳማንታ ፖወር የነጩ ወያኔዎች ቡድን ግንባር ቀደም ተሰላፊ ሲሆኑ፤ ቡድኑ በአሜሪካ ፖለቲካ ውስጥ ያለው ድርሻ ከፍተኛ ነው፡፡ ፖሊሲ በማውጣትም ሆነ የአገሪቱ መሪዎች ውሳኔ ለማስተላለፍ የሚረዱ መረጃዎች የሚቀርበው በአንድ ይሁን በሌላ መልኩ እነዚህ ሰዎች ናቸው፡፡

ከነጮቹ ወያኔዎች መካከል ስሟ በቀዳሚነት የሚጠቀሰው ጌል ስሚዝ ነች፤ ጌል ስሚዝ ከ40 ዓመት በላይ የዘለለ ከሕወሓት ጋር ግንኙነት አላት፡፡ እንደ አውሮፓዊኑ አቆጣጠር በ1970 መጀመሪያ ላይ በምስራቅ አፍረካ ፈሪላንስ ጋዜጠኛ በመሆን ሥራ የጀመረች ሲሆን በዓለም ዐቀፍ መድረክ ሕወሓትን ለመጀመሪያ ጊዜ ያስተዋወቀችው ይችው ሴት ነች፡፡

በኅዳር 1973 ከዛሬ 41 ዓመት በፊት ጌል ስሚዝ ዘ ክርስቲያን ሳይንስ ሞኒተር /The Christian science monitor/ ላይ ሕወሓትን በተመለከተ አንድ ሀተታ ጽፋ ነበር፡፡ በጽሑፏም በወቅቱ ቡድኑ በከፍተኛ ደረጃ እየተጠናከረ መሆኑን ገልፃ የቡድኑ ትልቁ ችግር የውጭ አገራት ድገፍ ማጣቱ ነው ስትል አገራት ለቡድኑ ድጋፍ እንዲያደርጉ ወትውታለች፡፡

በዛን ወቅት የአሜሪካ የስለላ ድርጅት ሲአይ ኤ በድኑን በአሸባሪነት ፈረጆ የነበረ ሲሆን፤ ይህ መዝገብ ተዘግቶ በወቅቱ ኢትዮጵያን ይመራ የነበውን የደርግ አስተዳደር እንዲወገድ ጊል ስሚዝ ከፍተኛ ሚና ተጫውታለች፡፡

በወቅቱ የነበራትን መሻቷን ለማሳካት ደግሞ ስለ ሕወሓት ቡድን በርካታ ጽሑፎችን በቢቢሲ፣ ዘ ጋርዲያን፣ ኔዮርክ ታይምስ እና ፋይናንሻል ታይምስ ላይ አስነብባለች፡፡

ጊል ስሚዝ ገና ጋዜጠኛ እያለች የተጣባት የወያኔ ፍቅር እሳካሁንም አብሯት ዘልቋል፤ የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት ዩኤስአይዲ ጨምሮ በርካታ ተቋማትን መምራት የቻለችው ጌል ስሚዝ የአሜሪካ መሪዎች ቢቀያየሩም ከሕወሓት ጋር ያላት ፍቅር ግን ለአንድ ቀንም ቢሆን ውልፊት ብሎ አያውቅም፡፡ይህንኑ እውነታ ደግሞ ራሷ በአደባባይ ስትናገረው ተደምጣለች፡፡

በቅርቡ እንኳን የአመሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒዮ ብሊንከን በኢትዮጵያ ላይ ጫና ለመፍጠር ወደ ኬንያ፣ ሴኔጋልና ናይጄሪያ ሲያቀኑ ይዘዋቸው ከመጡት የልዑክ አባላት መካክል አንዷ ጊል ስሚዝ ነች፡፡

ነጮቹ ወያኔዎች በዴሞክራቲክ ፓርቲ ውስጥ የተሰገሰጉ ሲሆን፤ በዓለም ዐቀፍ ደረጃ የተበዳይዋን ኢትዮጵያ እውነታ በመደበቅ የአሸባሪውን ሕወሓት ተበዳይ በማስመሰል የአሜሪካና ሌሎች አገራት ሕዝብን ለማጭበርበር የሚታትሩ ናቸው፡፡

በነጩ ቤተመንግሥት ካሉ ነጭ ወያኔዎች መካክል ዊንዲ ሼርማ ሌላኛዋ ናቸው፡፡ ይችህ ሴት በአሁኑ ወቅት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ምክትል በመሆን እየገለገሉ ሲሆን ከሕወሓቱ መራሽ መንግሥት ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያላቸው ነበሩ፡፡

በ2007 በኢትዮጵያ በተደረገው ምርጫ ኢሕአዴግ 100 በመቶ አሸንፎ ዓለም የተሳለቀበትን ምርጫ ቢያደርግም የአይጥ ምስክር ዲንቢጥ እንዲሉ ዊንዲ ሼርማ ለሕወሓት ጠብቅና በመቆም ምርጫው ፍትሓዊ እና ዴሞክራሲያዊ ነው ሲሉ ምስክርነታቸውን ሰጡ፡፡ በዚህ ንግግራቸው ደግሞ አሚኒስቲ እንተርናሽናልን ጨምሮ ሌሎች ተቋማት ከፍተኛ ትችትን ሰነዘሩባቸው፡፡

የሕወሓት ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አንድ አባል እስኪመስሉ ድረስ ለዚህ የሽብር ቡድን ሽንጣቸውን ገትረው የሚከራከሩት ሌላኛዋ ነጭ ወያኔ ሱዛን ራይስ ናቸው፡፡ በ1990ዎቹ የአፍሪካ ጉዳዮች ኃላፊ ሆነው ያገለገሉት ሱዛን ራይስ በወቅቱ ከሕወሓት ጋር የፈጠሩት ወዳጅነት እስከዛሬም የዘለቀ ነው፡፡

ሱዛን የአሜሪካ ባለሥልጣናት በምንም መልኩ ሕወሓትን የሚጎዳ ውሳኔን እንዳይወስኑ ትከላከላለች ታግባባለች፡፡ በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትርና የሽብር ቡድኑ መስራች መለስ ዜናዊ የቀብር ስነ ስርዓት ላይ በመገኘት መሪ ሙሾ አውራጅ የነበረችው ይህችው ሴት ነበረች፡፡

ዲፕሎማቱ ጄፍሪ ፊልትማን እና ሳማንታ ፖዎር ከነጮቹ ወያኔዎች ቡድን አባላት መካክል ሌሎቹ ሲሆኑ እነዚህ ሰዎች በተለያዩ የሥራ ኃላፊነት ላይ ቢገኙም በሕወሓት ጉዳይ ላይ ግን የተጠና እና የተቀናጀ ሥራን ይሰራሉ፡፡

ለሥራቸው ይረዳቸው ዘንድም በዓለም ዐቀፍ ደረጃ ሥም ያላቸውን መገናኛ ብዙኃን ይጠቀማሉ፡፡ ይህንን ሥራቸውን የሚያፋጥኑላቸው የሕወሓት ተቀላቢ ጸሐፍትን፣ አክቲቪስቶችንና ጋዜጠኞችን ያደረጁ ሲሆን ፀረ ኢትዮጵያ የሆኑ አቋሞችን የተለያዩ አጀንዳዎችን በመያዝ ያሰራጫሉ በዚህም አሜሪካዊያንን እና የዓለም ሕዝብን በማሳሳት ያለተገባ ውሳኔ በኢትዮጵያ ላይ እንዲተላለፍ ያደርጋሉ፡፡

መንግሥታት በተቀያየሩ ቁጥር አሜሪካ በአገራት ላይ ያላት የውጭ ፖሊሲ ባይቀያየርም የነጮቹ ወያኔዎች ዋነኛ ተግባር ግን በኢትዮጵያ ጉዳይ የአሜሪካ አጋር ሕወሓት ብቻ እንደሆነ ማቅረብ፣ ቡድኑ እየፈፀማቸው ያሉትን አረመኒያዊ ተግባር እንዳይጋለጡ መከላከልና ሽፋን መስጠት ነው፡፡

ይህንን በማድረግ ሕወሓት ከኢትዮጵያ በመዝረፍ የሚያደርሳቸውን ዶላር መስቀጠል ሲሆን፤ ኢትዮጵያዊያን ግን አሁን ለእንዲህ ዓይነቱ ዘረፋ እንግዳ አይደሉምና ከራሳችን ተዘርፎ የራሳችንን አገር ለማፍረስ ሴይጣንን በሚያስቀኑ ፍጥረታት የሚፈጠርን ቅንጅት በቃ ብለዋል፡፡

Via walta

Exit mobile version