” ከአዲሱ የኢትዮጵያ ካርታ ጋር ተያይዞ በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚሰራጨዉ መረጃ ተቀባይነት የሌለዉና መወገዝ ያለበት ነዉ።”-የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን
የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን በሃገር አቀፍ የጥናትና ምርምር ስራና በአጠቃላይ የኮሚሽኑ ሁኔታ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ዶ/ር ጣሰዉ ገብሬ ኮሚሽኑ እስካሁን ደረስ ሲሰራ የነበረዉን አጠቃላይ የጥናትና ምርምር ስራ አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል።
የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ከአስተዳደራዊ ወሰኖች: ከማንነትና ራስን በራስ ከማስተዳደር ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች ላይ ጥልቅ ጥናትና ምርምር በማድረግ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ምክረ ሃሳቦችን ለማዘጋጀትና ለማቅረብ የተቋቋመ ኮሚሽን ነዉ።
የኮሚሽኑ ሰብሳቢ እንደተናገሩት ከሰኔ 2012 ጀምሮ በአስተዳደር ወሰን: የማንነትና ራስን በራስ የማስተዳደር ጉዳዮች ላይ አገር አቀፍ የጥናትና ምርምር ስራ ሲያከናዉን እንደነበር ተናግረዋል።
ጥናትና ምርምሩ በፊንፊኔ ዩኒቨርስቲ ባለቤትነት የሚመራ መሆኑን የተናገሩት ሰብሳቢዉ ሌሎች ችግሮች ባሉባቸዉ አካባቢዎች 28 ዩኒቨርስቲዎች የተሳተፉበት መሆኑን ጠቅሰዋል።
በጥናቱ 56 ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች የተሸፈኑና 70 ተመራማሪዎችና በርካታ መረጃ ሰብሳቢዎች የተሳተፉበት መሆኑን የገለጹት ዶ/ር ጣሰዉ ገብሬ በተለያዩ ሁኔታዎች ማለትም በድርሳናት ዳሰሳ/ክለሳ: በቁልፍ መረጃ ሰጪ ቃለ ምልልስ: የትኩረት ቡድን ዉይይት እና ቤት ለቤት በታብሌት የታገዘ የቤተሰብ መረጃ መሰብሰቡን ጠቁመዋል።
በማንነት: ራስን በራስ በማስተዳደር: በአስተዳደር ወሰን እና የሕግና ፖሊሲ አማራጮች ዙሪያ አራት የተጠቃለለ የጥናትና ምርምር ሪፖርት መቅረቡንም ገልጸዋል።
በተደረገዉ ጥናትና ምርምር ዉስጥ ከመዋቅራዊ አደረጃጀት ጋር የተገናኘ ግኝት የሚተካተተበት መሆኑን እና በቀረበዉ ሃገራዊ የጥናት ዉጤት ላይ ተከታታይ የባለድርሻ አካላት ዉይይትና ግብአት በማካተትና በማዳበር ይፋ እንደሚደረግም በመግለጫቸዉ ጠቅሰዋል።
ጥናትና ምርምሩ ለ18 ወራት ሲካሄድ የነበረ ሲሆን ጥናትና ምርምር ለማካሄድ ከተመረጡ 68 ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች መካከል በ12 ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች በጸጥታ ችግሮችና በተያያዥ ምክንያቶች ጥናትና ምርምሩ አልተካተተም።
የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸዉ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ አዲሱ የኢትዮጵያ ካርታ ነዉ በማለት በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የተለቀቀዉ መረጃ መሠረተ ቢስና መወገዝ ያለበት ነዉ ብለዋል።
ወንድማገኝ አሰፋ
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ።… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
- “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረውየሚነሳው ጉዳዩ ልብ ሰባሪ ነው፣ ያስቃል፣ ያዝናናል፣ ያስገርማል፣ ያሳዝናል፣ ይቀፋል፣ ያሳፍራል፣ ለማመን ያስቸግራል … አንባቢ ስም… Read more: “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረው
- ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!በፖለቲካም ሆነ በአካባቢያዊ አጀንዳ ነፍጥ ያነገቡ እና ጦርነትን አማራጭ አድርገው የሚንቀሳቀሱ ኢ -መደበኛ አደረጃጀቶች ሁሉ የጦር… Read more: ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!