” ከአዲሱ የኢትዮጵያ ካርታ ጋር ተያይዞ በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚሰራጨዉ መረጃ ተቀባይነት የሌለዉና መወገዝ ያለበት ነዉ።”-የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን
የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን በሃገር አቀፍ የጥናትና ምርምር ስራና በአጠቃላይ የኮሚሽኑ ሁኔታ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ዶ/ር ጣሰዉ ገብሬ ኮሚሽኑ እስካሁን ደረስ ሲሰራ የነበረዉን አጠቃላይ የጥናትና ምርምር ስራ አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል።
የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ከአስተዳደራዊ ወሰኖች: ከማንነትና ራስን በራስ ከማስተዳደር ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች ላይ ጥልቅ ጥናትና ምርምር በማድረግ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ምክረ ሃሳቦችን ለማዘጋጀትና ለማቅረብ የተቋቋመ ኮሚሽን ነዉ።
የኮሚሽኑ ሰብሳቢ እንደተናገሩት ከሰኔ 2012 ጀምሮ በአስተዳደር ወሰን: የማንነትና ራስን በራስ የማስተዳደር ጉዳዮች ላይ አገር አቀፍ የጥናትና ምርምር ስራ ሲያከናዉን እንደነበር ተናግረዋል።
ጥናትና ምርምሩ በፊንፊኔ ዩኒቨርስቲ ባለቤትነት የሚመራ መሆኑን የተናገሩት ሰብሳቢዉ ሌሎች ችግሮች ባሉባቸዉ አካባቢዎች 28 ዩኒቨርስቲዎች የተሳተፉበት መሆኑን ጠቅሰዋል።
በጥናቱ 56 ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች የተሸፈኑና 70 ተመራማሪዎችና በርካታ መረጃ ሰብሳቢዎች የተሳተፉበት መሆኑን የገለጹት ዶ/ር ጣሰዉ ገብሬ በተለያዩ ሁኔታዎች ማለትም በድርሳናት ዳሰሳ/ክለሳ: በቁልፍ መረጃ ሰጪ ቃለ ምልልስ: የትኩረት ቡድን ዉይይት እና ቤት ለቤት በታብሌት የታገዘ የቤተሰብ መረጃ መሰብሰቡን ጠቁመዋል።
በማንነት: ራስን በራስ በማስተዳደር: በአስተዳደር ወሰን እና የሕግና ፖሊሲ አማራጮች ዙሪያ አራት የተጠቃለለ የጥናትና ምርምር ሪፖርት መቅረቡንም ገልጸዋል።
በተደረገዉ ጥናትና ምርምር ዉስጥ ከመዋቅራዊ አደረጃጀት ጋር የተገናኘ ግኝት የሚተካተተበት መሆኑን እና በቀረበዉ ሃገራዊ የጥናት ዉጤት ላይ ተከታታይ የባለድርሻ አካላት ዉይይትና ግብአት በማካተትና በማዳበር ይፋ እንደሚደረግም በመግለጫቸዉ ጠቅሰዋል።
ጥናትና ምርምሩ ለ18 ወራት ሲካሄድ የነበረ ሲሆን ጥናትና ምርምር ለማካሄድ ከተመረጡ 68 ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች መካከል በ12 ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች በጸጥታ ችግሮችና በተያያዥ ምክንያቶች ጥናትና ምርምሩ አልተካተተም።
የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸዉ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ አዲሱ የኢትዮጵያ ካርታ ነዉ በማለት በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የተለቀቀዉ መረጃ መሠረተ ቢስና መወገዝ ያለበት ነዉ ብለዋል።
ወንድማገኝ አሰፋ
- የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”በአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች መመስከራቸውን ቢቢሲ አስታወቀ። ይህ የተገለጸው… Read more: የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”
- በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነውለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ መያዙንna ለዚህም ተግባራዊነት ከሰባት ነጥብ… Read more: በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነው
- አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን ህብረቱ አረጋግጠአፍሪካ ህብረት የውጭ ምንዛሬ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር እንደሚያዘዋውር ተጠቅሶ በህብረቱ ስም የወጣው ዜና ሃሰት፣ ሆን… Read more: አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን ህብረቱ አረጋግጠ
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች
- የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋልየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ። የዕዳ ጫናውን ለማቃለል የባንክ ወልዱም… Read more: የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋል
- ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁመግቢያ ሽግግር ፍትህ ጉልህ የመብት ጥሰቶች በተፈፀመባቸው ሀገራት ተጠያቂነትን ለማስፈን እና ተበዳዮችን ለመካስ ጥቅም ላይ ሲውል… Read more: ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁ
- “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”“የሚሊሻ ኀይሉን በተመለከተ የሚዘዋወረው መረጃ ፍጹም መሠረተ ቢስ ነው” ሲሉ ኮሎኔል ግርማ ገሰሰ አስታወቁ። “ቅጥፈት ነው”… Read more: “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”
- “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን“የትግራይ ተወላጆች ትህነግ ለፈጸመው ወረራ፣ ዘረፋ፣ ማፈናቀልና የግድያ ተግባራት የተቀናጀ የፖለቲካና የሚዲያ ድጋፍ ሰጥተዋል። በተለይም በትግራይ… Read more: “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን
- የዜናው ሰም፣ ወርቅና “ትህነግ ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው ” የትህነግ ዜናውን አጣጣለለአንድ ቀን ከጮኸና አየሩን ሁሉ ከተቆጣጠረ በሁዋላ ውሃ የተቸለሰበት “ሕወሓት ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው” የሚለው… Read more: የዜናው ሰም፣ ወርቅና “ትህነግ ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው ” የትህነግ ዜናውን አጣጣለ