Site icon ETHIO12.COM

አማራ ክልል “ትህነግን ለመደምሰስ ሕዝብ ይዘጋጅ” አለ

ርእሰ መሥተዳድሩ በክልሉ የደረሰውን ውድመት ሲዘግቡ ለቆዩ የመገናኛ ብዙኀን ሙያተኞች ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ከአሁናዊ ሀገራዊ ሁኔታዎች አኳያ ጥያቄዎች ተነስተውላቸዋል። ❝አሁን ላይ ከአሸባሪው ትህነግ አባላት የእስር መፈታት ጋር ተያይዞ ሕዝቡ ሁኔታው ቢያስቆጣው ትክክል ነው ፤ እውነትም አለው፤ የቡድኑ አባላትም ወንጀለኝነታቸውን እናምናለን❞ ብለዋል።

የሽብር ቡድኑ አባላት ከታሰሩም በኋላ የቡድኑ ወረራ ተባብሶ የቀጠለና አሁንም ድረስ ለዳግም ወረራ እየተዘጋጀ በመሆኑ የአባላቱ መለቀቅና መታሰር ያለውን ሁኔታ ጋር ሲታይ የሽብር ቡድኑን ከመደምሰስ ዋና ዓላማ የሚያነጥል ጭንቀት ውስጥ የሚከት እንዳልሆነ ገልፀዋል።

❝አሁን ላይ ከአሸባሪው ትህነግ አባላት የእስር መፈታት ጋር ተያይዞ ሕዝቡ ሁኔታው ቢያስቆጣው ትክክል ነው ፤ እውነትም አለው፤ የቡድኑ አባላትም ወንጀለኝነታቸውን እናምናለን❞

ምንም እንኳን ሕዝቡ ከሀገራዊ አንድነትና ሰላም ፍላጎት አኳያ የቡድኑ አባላት መፈታት ቢያሰጋውም በተለይም የችግሩ ገፈት ቀማሽ የአማራ ሕዝብ በርካታ ችግሮች ያሉበት በመሆኑ ከጀመረው ሽብር ቡድኑን የማጥፋትና ኅልውናውን የማረጋገጥ ዘመቻ መዘናጋት የለበትም ብለዋል ርእሰ መሥተዳድሩ።

ቡድኑ እየወጋን ያለው ብቻውን አይደለም በተለይም ከቅማንት ጽንፈኛ ቡድን፣ ከጉምዝና ሸኔ ቡድኖች እንዲሁም ከውጭ እንደ ግብጽና ሌሎች አንዳንድ ሃገራት ጋር በመሆን ኢትዮጵያ እንዳትለማ ለማድረግና ለማውደም እየሰራ መሆኑን አንስተዋል።

ርእሰ መሥተዳድሩ የሽብር ቡድኑ ካልተወገደ እንደ አማራ ሕዝብም ይሁን እንደ ኢትዮጵያ ትልቅ ስጋት በመሆኑ የክልሉ መንግሥት ከፌደራል መንግሥት ጋር በመነጋገር ሽብር ቡድኑ በሚጠፋበትና የወደመው ሃብት በሚተካበት ልክ ይሠራል ብለዋል። ሆኖም ሕዝቡ በሚነሱ አንዳንድ ሐሳቦች ተበርዞ ሽብር ቡድኑን ከመደምሰስ ዐቢይ ዓላማው እንዳይነጠል አሳስበዋል ሲል አሚኮ ዘግቧል።


Exit mobile version