Site icon ETHIO12.COM

ትህነግ ጦርነት በከፈተበት ግንባር ሊቀርብለት የነበረ 500 ሺህ ሊትር ነዳጅ ተያዘ

አሸባሪው ህወሃት ጦርነት በከፈተበት ግንባር ናፍታ እና ቤንዚን ሊያቀብል የነበረ አይሱዙ ተሽከርካሪ በቁጥጥር ስር ዋለ።

መነሻውን ከሰመራ ያደረገ ኮድ 3 ታርጋ ቁጥር A47679 አይሱዙ ተሽከርካሪ መዳረሻውን ወደ አሸባሪው ህወሓት ቡድን በማድረግ 3000 /ሦስት ሺህ/ ሊትር ናፍጣ እና 2000 /ሁለት ሺህ/ ቤንዚል ካልዋን ላይ ሲደርስ በቁጥጥር ስር ውሏል።

በግዳጅ ቀጠናው የሚገኙት መ/አለቃ መንግስተአብ አበራ እንደተናገሩት በአሁኑ ሰዓት አሸባሪው ህወሓት በሀገራችን ላይ ጦርነት ቢከፍትም በጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን አፀፋዊ ምላሽ እየተሠጠ ባለበት ወቅት በህገ ወጥ መንገድ ለጠላት ሊደርስ የነበረን ነዳጅ መቆጣጠር ችለናል ብለዋል።

መ/አለቃ መንግስተአብ አበራ አክለውም በቀጣይም ለአሸባሪው የትህነግ ቡድን በህገወጥ መንገድ ሊደርስ የሚችል ማንኛውም ነገር ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በጋራ እንደሚሠሩ ተናግረዋል።

ምንላርግህ ሞሴ
ፎቶ ምንላርግህ ሞሴ Ethiopian Defence fb

Exit mobile version