Site icon ETHIO12.COM

ቀጣሪ ድርጅቶች ከግል የትምህርት ተቋማት የተመረቁ ተቀጣሪዎችን የትምህርት ማስረጃዎች ሕጋዊነት እንዲያረጋግጡ ተጠየቁ

የመንግሥትም ሆነ የግል ቀጣሪ ድርጅቶች ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተመረቁ ሠራተኞቻቸውን እና አዲስ ሠራተኞችን ከመቅጠራቸው በፊት የተቀጣሪዎቹን የትምህርት ማስረጃዎች ሕጋዊነት እና ትክክለኛነት መረጋገጥ እንደሚገባቸው የኢፌዴሪ ትምህርት እና ሥልጠና ባለሥልጣን አሳሰበ።

ተገልጋዮች ወይም ሕጋዊ ወኪሎች የማረጋገጫ አገልግሎት ለማግኘት ወደ ባለሥልጣኑ ከመሔዳቸው በፊት የሚከተሉትን መስፈርቶች በማሟላት አገልግሎቱን ማግኝት እንደሚችሉም ገልጿል።

መስፈርቶቹም፦

1. በጀርባው ላይ የኮሌጁ ኃላፊ እና ሬጅስትራር ፊርማ እና ማህተም ያለበት ኦሪጅናል ዲግሪ ከኮፒ ጋር በማያያዝ፤
2. በጀርባው ላይ የኮሌጁ ኃላፊ እና ሬጅስትራር ፊርማ እና ማህተም ያለበት ኦሪጅናል ትራንስክሪፕት/Student Copy/ ከኮፒ ጋር በማያያዝ፤
3. ዲግሪውን ለመማር በመግቢያነት የተያዘ ኦሪጅናል ዲፕሎማ ወይም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሰርቲፊኬት ከኮፒ ጋር በማያያዝ፤
4. ዲግሪውን ለመማር በመግቢያነት የተያዘው የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ከሆነ በትምህርት ምዘናዎች እና ፈተናዎች አገልግሎት ድርጅት ትክክለኛነቱ የተረጋገጠ ከኮፒ ጋር በማያያዝ፤
5. ዲግሪውን  ለመማር  በመግቢያነት የተያዘው ዲፕሎማ ከሆነ ዲፕሎማው  በተገኘበት ክልል የቴክኒክ እና ሙያ ኤጀንሲ ወይም የዞን/የከተማ መስተዳደር የሥራ እና ሥልጠና ቢሮ ትክክለኛነቱ የተረጋገጠ እንዲሁም የደረጃ 4 ብቃት  ማረጋገጫ(COC) ካገኙበት ማዕከል የተረጋገጠ መሆን አለበት ከኮፒ  ጋር በማያያዝ እና
6. የስም ለውጥ ካለ የፍርድቤት ውሳኔ ከኮፒ ጋር በማያያዝ ናቸው።
ዘገባ EBC

Exit mobile version