የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ2 ሺህ 700 በላይ አጠራጣሪ የፋይናንስ ማጭበርበር ጥቆማዎች እንደደረሱትና አንድ መቶ ሰባ ሰባቱን ለሕግ አካላት ማስተላለፉን ገለጸ። ይህ የተገለጸው አገልግሎቱ ከፌዴራል የፍትህና ህግ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር አዳማ ባዘጋጀው መድረክ ላይ ነው።
የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን አማረ እንደገለጹት አገልግሎቱ የሀገሪቷ የፋይናንስ ደህንነት ለማረጋገጥ ባንኮችና እንሹራንሶችን እንዲሁም ከማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራ ነው።
በተለይ በታክስ ማጭበርበር፣ ከህጋዊ የፋይናንስ ተቋማት ውጭ የሚንቀሳቀስ የውጭ ምንዛሪ ዙሪያ ከፍትህ ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብርና ቅንጅት እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
በዚህም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከቀረቡት 2 ሺህ 700 አጠራጣሪ የፋይናንስ ጥቆማዎች ውስጥ 177 የሚሆኑትን አጠራጣሪ ጥቆማዎች በመለየትና በመተንተን ለህግ አካላት ማስተላለፉን ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።
በተጨማሪም በህገ ወጥ መንገድ የተገኘውን ገንዘብ ህጋዊ አስመስሎ መጠቀም ወንጀሎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ከ166 አገሮች ጋር መረጃ መለዋወጥ ተችሏል ብለዋል።
የተቋሙን አሰራር የማሻሻልና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ ሪፎርም በመከናወን ላይ እንደሚገኝም አቶ ሙለቀን ተናግረዋል። መድረኩ ተግባር ተኮር የሆነ የፋይናንስ ደህንነትን ማረጋገጥ፣ በዘርፉ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥርም ገልጸዋል።
የፌዴራል የፍትህና ህግ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዘካርያስ ኤርጉላ በበኩላቸው ተቋሙ የሀገሪቱን የፋይናንስ ደህንነት ለማረጋገጥ በኦፕሬሽንና ወንጀሎችን በጋራ መከላከል ላይ በትብብር እንደሚሰራ አስታውቀዋል።
በዚህም ሽብርን በገንዘብ መደገፍና በህገ ወጥ የተገኘውን ገንዘብና ሀብት ህጋዊ አስመስሎ መጠቀም ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በጋራ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።
”ህግን ማስከበርና ወንጀልን ከመከላከል አንፃር ከአገልግሎቱ ጋር በቅንጅት እንሰራለን” ያሉት ምክትል ዳይሬክተሩ፤ ከፖሊስ፣ ከአቃቤ ህግ፣ ከባንኮችና ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመሆን ተባብረው እንደሚሰሩም ተናግረዋል።
መድረኩ የዘመኑን የቴክኖሎጂና ስልቶችን በመጠቀም በፋይናንስ ዙሪያ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን በቅንጅት ለመከላከል ያግዛል ያሉት አቶ ዘካርያስ፣ ከፋይናንስ ውጭ በማዕድን፣ በብረታ ብረትና ሌሎች ሀብቶች ላይ ጭምር የሚፈፀሙ የማጭበርበርና የቅሸባ ወንጀሎችን ለመከላከል በጋር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
በመድረኩ ላይ ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት፣ ከፍትህና ህግ ማስከበር የተውጣጡ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች በስሟ የሚገዘቱት እንጀራዋን ለመብላት እንጂ መከራዋን ለመካፈል አይደለም፤ በተቃራኒው እንጀራዋን በልተው ተረከዛቸውን አነሡባት” ሲሉ ጠቅላይ… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤ ወንጌላዊ መኾን መልካም ነው፣ ወንጀለኛ መኾን ግን ሐጥያት ነው ብለዋል፡፡ እህትና ወንድም፣ እናትና አባትን አጎሳቁሎ ገንዘብ… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣ እንዲሁም ትኩረቴ በቀላሉ ይከፋፈል ነበር። ሐኪሜ የብረት ማዕድን አዘዘልኝ። ኪኒኖቹን መውሰድ ጀመርኩ፤ አመጋገቤንም አስተካከልኩ። ብዙም ሳይቆይ… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን ለጎን የትግራይ ከፍተኛ ባለስልጣናትና የዞን አስተዳዳሪዎች የተባሉ ሁለት ዓይነት መረጃዎች እየሰጡ ነው። መንግስት ግን… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች ዜና የሚያቀብሉና እነሱኑ የሚከተሉ ስምምነቱ መክሸፉንና መንግስት ውሉን እንደተወው፣ የሶማሌ ማንግስትም መንግስት በአደባባይ ስምምነቱን… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን ዋስትና አፀና። ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎቹ ከሀገር እንዳይወጡ እግድ እንዲጣል ትዕዛዝ ሰጥቷል። ተጠርጣሪዎቹ የቀድሞ የህዝብ ትራንስፖርት የተሽከርካሪ… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት ውስጥ የሚኖሩ ዜጎቹን መልሶ ለመቀበል ያሳየው ተባባሪነት አናሳ መሆኑን ካውንስሉ ባደረገው ግምገማ ስለተገነዘበ” ነው። “የኢትዮጵያ ባለሥልጣኖች… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ