የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ2 ሺህ 700 በላይ አጠራጣሪ የፋይናንስ ማጭበርበር ጥቆማዎች እንደደረሱትና አንድ መቶ ሰባ ሰባቱን ለሕግ አካላት ማስተላለፉን ገለጸ። ይህ የተገለጸው አገልግሎቱ ከፌዴራል የፍትህና ህግ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር አዳማ ባዘጋጀው መድረክ ላይ ነው።
የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን አማረ እንደገለጹት አገልግሎቱ የሀገሪቷ የፋይናንስ ደህንነት ለማረጋገጥ ባንኮችና እንሹራንሶችን እንዲሁም ከማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራ ነው።
በተለይ በታክስ ማጭበርበር፣ ከህጋዊ የፋይናንስ ተቋማት ውጭ የሚንቀሳቀስ የውጭ ምንዛሪ ዙሪያ ከፍትህ ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብርና ቅንጅት እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
በዚህም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከቀረቡት 2 ሺህ 700 አጠራጣሪ የፋይናንስ ጥቆማዎች ውስጥ 177 የሚሆኑትን አጠራጣሪ ጥቆማዎች በመለየትና በመተንተን ለህግ አካላት ማስተላለፉን ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።
በተጨማሪም በህገ ወጥ መንገድ የተገኘውን ገንዘብ ህጋዊ አስመስሎ መጠቀም ወንጀሎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ከ166 አገሮች ጋር መረጃ መለዋወጥ ተችሏል ብለዋል።
የተቋሙን አሰራር የማሻሻልና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ ሪፎርም በመከናወን ላይ እንደሚገኝም አቶ ሙለቀን ተናግረዋል። መድረኩ ተግባር ተኮር የሆነ የፋይናንስ ደህንነትን ማረጋገጥ፣ በዘርፉ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥርም ገልጸዋል።
የፌዴራል የፍትህና ህግ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዘካርያስ ኤርጉላ በበኩላቸው ተቋሙ የሀገሪቱን የፋይናንስ ደህንነት ለማረጋገጥ በኦፕሬሽንና ወንጀሎችን በጋራ መከላከል ላይ በትብብር እንደሚሰራ አስታውቀዋል።
በዚህም ሽብርን በገንዘብ መደገፍና በህገ ወጥ የተገኘውን ገንዘብና ሀብት ህጋዊ አስመስሎ መጠቀም ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በጋራ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።
”ህግን ማስከበርና ወንጀልን ከመከላከል አንፃር ከአገልግሎቱ ጋር በቅንጅት እንሰራለን” ያሉት ምክትል ዳይሬክተሩ፤ ከፖሊስ፣ ከአቃቤ ህግ፣ ከባንኮችና ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመሆን ተባብረው እንደሚሰሩም ተናግረዋል።
መድረኩ የዘመኑን የቴክኖሎጂና ስልቶችን በመጠቀም በፋይናንስ ዙሪያ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን በቅንጅት ለመከላከል ያግዛል ያሉት አቶ ዘካርያስ፣ ከፋይናንስ ውጭ በማዕድን፣ በብረታ ብረትና ሌሎች ሀብቶች ላይ ጭምር የሚፈፀሙ የማጭበርበርና የቅሸባ ወንጀሎችን ለመከላከል በጋር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
በመድረኩ ላይ ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት፣ ከፍትህና ህግ ማስከበር የተውጣጡ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
- የባህር ዳር ነዋሪዎች- ኢትዮጵያን ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር ማድረግ ይገባልየባህር ዳር ነዋሪዎች የሕዝብን ጥያቄ የመፍታት አቅም፣ ፍላጎት እና ቅንነት ያለው አመራር በመፍጠር ሕዝብን መካስ እንደሚያስፈልግ፣ ኢትዮጵያ በዘር ከመገፋፋት እና ከመጠቃቃት ነጻ የኾነች ፣ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር እንድትኾን ማድረግና የፌዴራል መንግሥት የአማራ ሕዝብ ኅብረ ብሔራዊ እና ልማት ወዳድ እንጅ ጦርነትን የማይፈልግ መኾኑን በውል በመገንዘብ የሕዝቡን ተዘዋውሮ የመሥራት እና … Read moreContinue Reading
- ለወልቃይት ጠገዴ ሴቲት ሁመራ አንድ ሚሊዮን የጉልበት ሰራተኛ ይፈለጋል፤ ከአንድ ነጥን አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ሰሊጥ ይጠበቃል“ከየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል አስተማማኝ ሰላም ያለው እዚህ ነው። ለሰራተኞች እንደ ቤተሰብ ዝግጅት አድርገናል። ኑ” ሲሉ የተሰሙት አምስት መቶና ሶስት መቶ ሄክታር ሰሊጥና ማሽላ ያመረቱ ባለሃብቶች ናቸው። የዞኑ ግብርና ቢሮ ሃላፊ እንዳሉት አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺህ ኩንታል የሰሊጥ ምርት ስለሚጠበቅ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሰራተኛ ሃይል ያስፈልጋል። የዞኑ አርባ … Read moreContinue Reading
- የጎንደርን ከተማ ምን አይነት ተኩስ እንደሌለ ተገለጸ፤ ጎንደር ተይዛለች ተብሎ ነበር“ጎንደር ከተማን ሙሉ በሙሉ ይዘናታል” ሲሉ ስማቸው እንዳይገለጽ ጠይቀው ለጀርመን ድምጽ መረጃ በሰጡ የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ፋኖ ቃል አቀባይ አየር ማረፊያውን ሆን ብለው እንዳልያዙ አመልክተዋል። እሳቸው ተናገሩ የተባለው በጀርመን ድምጽ እየተሰማ በለበት ሰዓት በተመሳሳይ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ውጊያ መደረጉን ሳያስተባብል ከተማዋን ለመያዝ የገባው ሃይል መደምሰሱን አሃዝ ጠቅሶ አመልክቷል። አገር መከላከያም … Read moreContinue Reading
- “የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ፣ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ”የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ (ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ) የሚለው የቆየ ተረት ልብን የሚያደማ ኩነትን ማሳያ ነው። እቺ መከረኛ ሚስት ባልዋ በእናቷ ልጅ ወንድሟ ተገደለ። ሟች ባል፣ ገዳይ ወንድም … ኢህአፓ “ሃይማኖት ነው” በሚል ሲገልጸው በነበረው ትግል በቀይና ነጭ ሽብር ስም እናቶች የወላድ መካን ሆነዋል። ጧሪ ያጡና ባዶ ቤት ሃዘን … Read moreContinue Reading
- U.S Senator Robert Menendez, His Wife, and three businessmen charged with bribery offensesU.S. Attorney Damian Williams said: “As the grand jury charged, between 2018 and 2022, Senator Menendez and his wife engaged in a corrupt relationship with Wael Hana, Jose Uribe, and Fred Daibes – three New Jersey businessmen who collectively paid hundreds of thousands of dollars of bribes, including cash, gold, … Read moreContinue Reading
- በአማራ ክልል የተነሳው ጦርነት በሰላም ሊቆጭ እንደሚችል ተሰማበአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ጦርነት በሰላማዊ መንገድ የሚቋጭበት አግባብ ተስፋ ሰጪ ደረጃ መድረሱ ተሰማ። የኢትዮ12 የዜና አቀባዮች እንዳሉት ሰላም ወደድ የሆኑ ዜጎች ችግሩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እያደረጉ ያለው ጥረት ውጤታም እየሆነ መሆኑንን ነው ያመለከቱት። በሰላም ጥረቱ ውስጥ የሚሳተፉትን ወገኖችና የሰላም ንግግር አመቻች የሆኑትን ክፍሎች ሳይጠቅሱ የዜናው ሰዎች እንዳሉት ጥረቱ ብዙ መንገድ … Read moreContinue Reading
- በትግራይ ሶስት ልጆቻቸውን ያጡ እናት ትህነግ በይፋ መርዶ ከማወጁ በፊት ህይወታቸው አጠፉ“ሶስት ልጆቼን ካጣሁ እኔ ምን አለኝ” ብለው ራሳቸውን በገመድ አንቀው ገደሉ፤ ዛሬም በውጭ አገር ተቀምጠው እናቶቻቸውን በእንግድነት እየጋበዙ የሚምነሸነሹ፣ አገሪቱን በጦርነት እየማገዱ ነው፤ ይህ ትምህርት ሆኖ እንድናስብ ካልደረገ ምን … ትግራይ ውስጥ ተቀስቅሶ ወደ ሌሎች ክልሎች በተስፋፋው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት “በሺዎች የሚቆጠሩ” የኢትዮጵያ ልጆች ሞተዋል። በመልሶ ማጥቃሩ በተለይ የትግራይ ተዋጊዎች … Read moreContinue Reading