አርተፊሻል ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ኢትዮጵያ የባህር በር ሊኖራት ይችላል፤ ይህ በአለም ላይ በኢትዮጵያ የአፋር ምድር ረባዳነት የተነሳ ተፈጥሮ የሰጠው እድል ነው!
በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል አርተፊሻል ቦይ በመስራት ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት መሆን ትችላለች፡፡ እንደዚህ አይነት አጋጣሚ ሊፈጠር የቻለው፤ የኢትዮጵያ የአፋር ቦታ ከባህር ወለል በታች እስከ 110 ሜትር ዝቅ የሚል በመሆኑ ምክንያት ነው፡፡
እንደዚህ አይነት ከባህር ወይም ከውቅያኖስ በዚህ አጭር እርቀት ያነሰ የወለል ዝቅታ (surface elevation) በዚህ ቦታ እንጂ በአለም ላይ የለም፡፡ በዚህ ጥሩ ተፈጥሮ የተነሳ ከቀይ ባህር ጋር ለማገናኘት ቦይ በመስራት ከመገናኘት ባሻገር የጣናን ሶስት እጥፍ የሚረዝም ሐይቅ በድንበሩ መፍጠር ይቻላል፡፡
የሚገነባው ቦይ 470 ሜትር ስፋት የሚኖረው ሲሆን፤ የአለማችን ትልቁን 124 ሜትር ስፋት ያለውን መርከብ በሁለት አቅጣጫ እንዲያስተናግድ በማሰብ እና መርከቡ የሚኖረው 34 ሜ የውሃ ውስጥ ጥልቀት ታሳቢ በማድረግ ነው፡፡ በዚህ መሰረት ቦዩ በአጠቃላይ 470 ሜትር ስፋት እና በትንሹ 50 ሜትር ጥልቀት ሊኖረው ይችላል፡፡
78 ኪሜ እርዝመት እና 470 ሜትር ስፋት ያለው አርተፊሻል ቦይ በሚሰራበት ወቅት፤ የቀይ ባህርን ውሃ ወደ ኢትዮጵያ ለመቀልበስ፤ ከ78 ኪሜ የኤርትራ መሬት ውስጥ 40 ኪሜ ላይ ብቻ የተወሰነ የማይጋነን ጥልቀት ያለው ቁፋሮ (excavation) የሚሰራ ይሆናል፡፡
ይህንን አርተፊሻል ቦይ በመስራት ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር ጋር መገናኘት ትችላለች፡፡ ሌላ ወደብ አልባ ሐገር በሚኖረው ተራራማና ከፍ ያለ የመሬት ተፈጥሮ የተነሳ ይህንን እድል ሊያገኝ አይችልም፡፡ ኢትዮጵያ ሌላ የወደብ አማራጭ ከኤርትራ ቢኖራትም ባይኖራትም፤ ይህንን ቦይ መገንባቱ የባህር በር ከማገኘትና ከኢኮኖሚ ጠቀሜታ ባሻገር ለአከባቢው ተፈጥሮ የሚጠቅም ነው ብዬ አስባለው፡፡
የመሬቱን አቀማመጥ (Orginal Ground Level x,y,z OGL data) በሰርቨየር በማንበብ እና የቦይ ግንባታ design manual በመጠቀም በዝርዝር ዲዛይን በማድረግ የግንባታ ወጪውን ተምኖ መገንባት ይቻላል፡፡ እኔ ቦይ አዋጪ በሆነ መንገድ ሊሰራ እንደሚችል እና preliminary design ነው ያቀረብኩት፡፡
ኤርትራ ኢትዮጵያ ላይ ከባህር ዳርቻ አንጻር በበደለችው በደል ላለፉት 30 አመታት ወጣቶቿን ሳዋ ወታደራዊ ማሰልጠኛ እያስገባች፤ ከነገ ዛሬ በኢትዮጵያ ተወረርኩ እያለች በስቅቅ እየኖረች እንደሆነ ይታወቃል፤ ኢትዮጵያም የአሰብ ወደብ የሚገኝበት የአፋር ግዛቷን ለማስመለስ ጥሩ ቀን እየጠበቀች ትገኛለች፡፡
ስለዚህ ያለውን የሁለቱ ሐገሮች ውጥረት በተወሰነ ደረጃ የአርተፊሻል ቦይ ግንባታው ይቀንሳል ብዬ አምናለሁ፡፡ የፕሮጀክት ግንባታ ወጪውም፤ ኢትዮጵያ ለጅቡቲ የምትከፍለውን አመታዊ የወደብ ኪራይ ግማሽ ወይም ሙሉ ቢያክል ነው፡፡ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ እንደ ጥሩ ወዳጅ እና ጎረቤት ሐገሮች ባህሩን በነጻነት ቢጠቀሙ ያተርፋሉ ባይ ነኝ!
በ Andinet Zeleke Bekele.
- ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋገጡ፤ በትግራይ አስተዳደር ስም ማስተባበያም አውጥተዋልበሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አካላት የሚዳክሩበት በዚህ ጦርነት የትግራይ… Read more: ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋገጡ፤ በትግራይ አስተዳደር ስም ማስተባበያም አውጥተዋል
- Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?Mercenaries from Ethiopia’s Tigray People’s Liberation Front are fighting alongside Sudanese army regulars against fighters of the Rapid Support Forces (RSF), the paramilitary… Read more: Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?
- Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAFSudanese warring party Rapid Support Forces has officially accused the Tigray People’s Liberation Front Fighters of fighting in Sudan in support of the… Read more: Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAF
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች በስሟ የሚገዘቱት እንጀራዋን ለመብላት እንጂ… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤ ወንጌላዊ መኾን መልካም ነው፣ ወንጀለኛ መኾን… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ