አርተፊሻል ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ኢትዮጵያ የባህር በር ሊኖራት ይችላል፤ ይህ በአለም ላይ በኢትዮጵያ የአፋር ምድር ረባዳነት የተነሳ ተፈጥሮ የሰጠው እድል ነው!
በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል አርተፊሻል ቦይ በመስራት ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት መሆን ትችላለች፡፡ እንደዚህ አይነት አጋጣሚ ሊፈጠር የቻለው፤ የኢትዮጵያ የአፋር ቦታ ከባህር ወለል በታች እስከ 110 ሜትር ዝቅ የሚል በመሆኑ ምክንያት ነው፡፡
እንደዚህ አይነት ከባህር ወይም ከውቅያኖስ በዚህ አጭር እርቀት ያነሰ የወለል ዝቅታ (surface elevation) በዚህ ቦታ እንጂ በአለም ላይ የለም፡፡ በዚህ ጥሩ ተፈጥሮ የተነሳ ከቀይ ባህር ጋር ለማገናኘት ቦይ በመስራት ከመገናኘት ባሻገር የጣናን ሶስት እጥፍ የሚረዝም ሐይቅ በድንበሩ መፍጠር ይቻላል፡፡
የሚገነባው ቦይ 470 ሜትር ስፋት የሚኖረው ሲሆን፤ የአለማችን ትልቁን 124 ሜትር ስፋት ያለውን መርከብ በሁለት አቅጣጫ እንዲያስተናግድ በማሰብ እና መርከቡ የሚኖረው 34 ሜ የውሃ ውስጥ ጥልቀት ታሳቢ በማድረግ ነው፡፡ በዚህ መሰረት ቦዩ በአጠቃላይ 470 ሜትር ስፋት እና በትንሹ 50 ሜትር ጥልቀት ሊኖረው ይችላል፡፡
78 ኪሜ እርዝመት እና 470 ሜትር ስፋት ያለው አርተፊሻል ቦይ በሚሰራበት ወቅት፤ የቀይ ባህርን ውሃ ወደ ኢትዮጵያ ለመቀልበስ፤ ከ78 ኪሜ የኤርትራ መሬት ውስጥ 40 ኪሜ ላይ ብቻ የተወሰነ የማይጋነን ጥልቀት ያለው ቁፋሮ (excavation) የሚሰራ ይሆናል፡፡
ይህንን አርተፊሻል ቦይ በመስራት ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር ጋር መገናኘት ትችላለች፡፡ ሌላ ወደብ አልባ ሐገር በሚኖረው ተራራማና ከፍ ያለ የመሬት ተፈጥሮ የተነሳ ይህንን እድል ሊያገኝ አይችልም፡፡ ኢትዮጵያ ሌላ የወደብ አማራጭ ከኤርትራ ቢኖራትም ባይኖራትም፤ ይህንን ቦይ መገንባቱ የባህር በር ከማገኘትና ከኢኮኖሚ ጠቀሜታ ባሻገር ለአከባቢው ተፈጥሮ የሚጠቅም ነው ብዬ አስባለው፡፡
የመሬቱን አቀማመጥ (Orginal Ground Level x,y,z OGL data) በሰርቨየር በማንበብ እና የቦይ ግንባታ design manual በመጠቀም በዝርዝር ዲዛይን በማድረግ የግንባታ ወጪውን ተምኖ መገንባት ይቻላል፡፡ እኔ ቦይ አዋጪ በሆነ መንገድ ሊሰራ እንደሚችል እና preliminary design ነው ያቀረብኩት፡፡
ኤርትራ ኢትዮጵያ ላይ ከባህር ዳርቻ አንጻር በበደለችው በደል ላለፉት 30 አመታት ወጣቶቿን ሳዋ ወታደራዊ ማሰልጠኛ እያስገባች፤ ከነገ ዛሬ በኢትዮጵያ ተወረርኩ እያለች በስቅቅ እየኖረች እንደሆነ ይታወቃል፤ ኢትዮጵያም የአሰብ ወደብ የሚገኝበት የአፋር ግዛቷን ለማስመለስ ጥሩ ቀን እየጠበቀች ትገኛለች፡፡
ስለዚህ ያለውን የሁለቱ ሐገሮች ውጥረት በተወሰነ ደረጃ የአርተፊሻል ቦይ ግንባታው ይቀንሳል ብዬ አምናለሁ፡፡ የፕሮጀክት ግንባታ ወጪውም፤ ኢትዮጵያ ለጅቡቲ የምትከፍለውን አመታዊ የወደብ ኪራይ ግማሽ ወይም ሙሉ ቢያክል ነው፡፡ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ እንደ ጥሩ ወዳጅ እና ጎረቤት ሐገሮች ባህሩን በነጻነት ቢጠቀሙ ያተርፋሉ ባይ ነኝ!
በ Andinet Zeleke Bekele.
- Ethiopia Working To Secure New Development Bank MembershipThe Ministry of Foreign Affairs disclosed that Ethiopia is working hard to become member of BRICS’ New Development Bank. In a media briefing… Read more: Ethiopia Working To Secure New Development Bank Membership
- የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”በአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች መመስከራቸውን ቢቢሲ አስታወቀ። ይህ የተገለጸው ከአለማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ከሃምሳ… Read more: የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”
- በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነውለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ መያዙንna ለዚህም ተግባራዊነት ከሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊየን በላይ ችግኝ መዘጋጀቱን ተገለጸ። 1… Read more: በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነው
- አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠአፍሪካ ህብረት የውጭ ምንዛሬ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር እንደሚያዘዋውር ተጠቅሶ በህብረቱ ስም የወጣው ዜና ሃሰት፣ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ መሆኑን መንግስት አስታወቀ። መረጃው ቀድሞውንም… Read more: አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠ
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ። አሁን ምኑ ነው አፍሪካ ህብረትን… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች