Site icon ETHIO12.COM

ኮንትሮባንድ – ከቁም እንስሳት ኢትዮጵያ ታገኝ የነበረው ገቢ ከ150 ሚሊዮን ወደ አስራ ሰባት ሚሊዮን ዶላር ወረደ

ኮንትሮባንድ ክፉኛ ከሚፈታተነው የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ገቢ ምንጮች መካከል የቁም እንሳሳት ንግድ አንዱ ነው። ዘርፉ በከፍተኛ ደረጃ በኮንትሮባንድ ንግድ በትሥሥር ዝርፊያ የሚፈጸምበት ሲሆን ጎረቤት አገሮችን በመጠቀም እንደሚከናውን በስፋት ሲነገር ቆይቷል።

ኢትዮጵያ በቀንድ ከብት ከአፍሪካ አንደኛ ከዓለም ደግሞ አምስተኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ ቢሆንም

ዛሬ ይፋ ሲደረግ እንድተሰማው ባለፉት ስምንት ዓመታት ከቁም እንስሳት ንግድ የሚገኘው የውጭ ምንዛሬ ክፉኛ አቆልቁሏል። ቀደም ሲል ከዘርፉ እስከ 150 ሚሊየን ዶላር የሚጠጋ ገቢ ይገኝበት የነበረው የቀንድ እንስሳት ንግድ፣ በ2014ና በ2015 ዓ.ም ገቢው ወደ 17 ሚሊየን ዶላር አሽቆልቋሏል። ምክንያቶቹ በጥናት አቅራቢዎቹ በዝርዝር ይፋ ስለመሆናቸው ኢዜአ ባይጠቅስም፣ ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ አካላት ቀደም ሲል ታጣቂ ሃይሎችን የሚያደራጁ፣ የሚያስታጥቁና የሚያሰማሩ ” ወዳጅ የሚባሉ አገራት” ዝርፊያውን አዲስ አበባ ተቀምጠው ከሚመሩት መካከል ቅድሚያ የሚጠቀሱ ናቸው።

ቀደም ሲል ከፍተኛ የቀንድ ከብት ባለበት የአገሪቱ ክፍል የሚነቀሳቀሱ የብሄር ስም ያላቸው ታጣቂዎች የቀንድ ከብቶችን ወደ ድንበር እንደሚነዱ ጠቅሰን መዘገባችን ይታወሳል። ከብቶቹም በሶማሌ ወደብ በኩል እንደሚሻገሩ ጥቆማ የሰጡት አስታውቀው ነበር። መንግስት ሃይሉን በሙሉ ድንበር በመጠበቅና የዝርፊያ ሰንሰለቱን እንዳይዘጋ እነዚሁ አካላት በብሄር ነጻ አውጪ ስም እዛና እዚህ ጦርነት፣ ግጭትና አለመረጋጋት በመፍጠር የመንግስትን አቅም እንደሚበታትኑ በዜናው ተጠቁሞ ነበር።

Exit mobile version