Site icon ETHIO12.COM

የትግራይ ህዝብን እንርዳ

ህወሓት በከፈተው ጦርነት ለህዝቡ የማያስብ የህወሓት አመራር፣ እኔ ስልጣን ከለቀኩ የትግራይ ህዝብም ይጥፋ በሚል መሰሪ ፖለቲካዊ ውሳኔው፣ የትግራይን ህዝብ ከሚኖርበት ቀይ እንዲፈናቀል ንብረቱም እንዲወድም አድርገዋል፣ የህወሓት አመራሮች ለአቅመ አዳም ያልደረሱ የትግራይ ወጣቶችን በማሰለፍ፣ በመጨረሻ ዋጋ ለሌለው ጦርነት ሚስኪኑ የትግራይ ወጣት አስገድሎ አብዛኛው የህወሓት አመራር እጁን ሰጥተዋል። ስብሓት ነጋ እና ቤተሰቡ ራሱ አድኖ እጁ ሲሰጥ ሚስክንዋ የትግራይ እናት ግን የልጅዋን መርዶ እየጠበቀች ይገኛል።

በዚህ ጦርነት ምክንያት የተጎዳው የትግራይ ህዝብ ነው፣ የትግራይ ህዝብ ተፈናቅለዋል፣ የግልም ይሁኑ የመንግስት ሰራተኞች ያለ ስራ ይገኛሉ፣ ደሞዝ እስካሁን ድረስ አለተከፈላቸውም፣ በገጠሩ የትግራይ አከባቢ ብዙ ሰው በርሃብ እየሞተ ይገኛል፣ ከአርባ ሺ በላይ የምእራብ ትግራይ ነዋሪዎች ወደ ሱዳን ተሰደዋል፣ ይህ ሁሉ ግፍ ህወሓት በሚከተለው የዘር ፖለቲካ የደረሰ ነው፣ ስለሆነም በመላው አለም የምትገኙ ኢትዮጲያውያን የትግራይን ህዝብ ከዚህ ሁሉ ችግር ትታደጉት ዘንድ በ አክብሮት እንጠይቃለን፣ ርሃብ ጊዜ የማይሰጥ ስለሆነ ቢያንስ ሊተርፍ የሚችለውን ሂወት እናትርፍ፣ ኢትዮጲያዊነታችንን በቅርቡ ሙሉ በሙሉ ይመለሳል። ይህ እርዳታ በቀጥታ ለትግራይ ተጎጂዎች የሚደርስ ነው..
.
የትግራይ ልማት ማህበር እና የትግራይ ዳያስፖራ ያሰባሰቡትን ገንዘብ 2.5 ሚልዮን ዶላር ህወሓት ወደ ስልጣን እስካልተመለሰ ድረስ ገንዘቡን አናንቀሳቅስም ብለው የትግራይ ህዝብ በርሃብ እየሞተ ገንዘቡን ይዘው ቁጭ ብለዋል፣ ህወሓቶች እና የህወሓት ደጋፊዎች በትግራይ ህዝብ ላይ ይህን ያክል ይጨክናሉ፣ ይህንን ታሳቢ አድርገን በፍጥነት እርዳታ ለግሰን የትግራይን ህዝብ እንታደገው።.

ጎፈንድሚ ከጥቂት ሰአታት ቦሃላ ለሁልም ክፍት አደርጋለሁኝ ከምስጋና ጋር.

ናትናኤል አስመላሽ
አሜሪካ

Exit mobile version