Site icon ETHIO12.COM

የመከላከያ ሰራዊት አባል መሆን አገርንና ሕዝብን ማገልገል ነው … ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ

የአገር መከላከያ ሰራዊት አባል መሆን አገርንና ሕዝብን ማገልገልና ጀግኖችን መቀላቀል ነው ሲሉ ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ ተናገሩ።

ወጣቶች ወደ ውትድርና ሙያ በመግባት ለአገርና ለሕዝብ ክብር መቆም አለባቸው ብለዋል።

ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ ከመከላከያ ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቆይታ የአገር መከላከያ ሰራዊት በትግራይ ክልል የሕግ ማስከበር እርምጃ ተጋድሎ በመፈጸም አገራዊ ተልዕኮውን መወጣቱን ገልጸዋል።

ሰራዊቱ በሕግ ማስከበር እርምጃው የተሰጠውን ተልዕኮ በስኬት በማጠናቀቅ የአገር አለኝታነቱን ማሳየቱንም ተናግረዋል።

“ሰራዊቱ በጀግኖች የተሞላ ነው፤ የዚህ ሰራዊት አባል መሆን የጀግኖች አባልና መሪ ከመሆን ባለፈ ክብር የሚያጎናጽፍ ነው” ሲሉም ገልጸዋል።

ማንኛውም ሰው በየትኛውም መስክ ጀግና መሆን ይፈልጋል ያሉት ሌተናል ጄኔራሉ የመከላከያ ሰራዊት አባል መሆን ደግሞ ጀግንነትን የሚያላብስ እንደሆነ አመልክተዋል።

በሰራዊቱ አባል ሆኖ ሕዝብን ማገለግል ትልቅ ክብር መሆኑን በመግለጽ፤ የኢትዮጵያ ወጣቶች የውትድር ሙያ ዋና ተግባር አገርና ሕዝብን ማገልገል መሆኑን አውቀው ሙያውን እንዲቀላቀሉና የኢትዮጵያ ወታደር የመሆን እድልን እንዲጠቀሙበት ጥሪ አቅርበዋል።

የአገር መከላከያ ሰራዊት ራሱን ለማዘመን የማሻሻያ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም መግለጻቸውን ከመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽን ዋና ዳይሬክቶሬት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ በትግራይ ክልል በተካሄደው የሕግ ማስከበር እርምጃ በራያ በኩል ያለውን ግንባር ሲመሩ እንደነበር የሚታወስ ነው።

የካቲት

Via (ኢዜአ)

Exit mobile version