ቀደም ሲል መንግስት እያለ የአሜሪካ መንግስት ከሽብረተኞች መዝገብ ውስጥ ያልፋቀውና በቅርቡ ፓርላማ ከኦነግ ሸኔ ጋር አሸባሪ ብሎ የሰየመው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ትህነግ፣ ሃያ ሁለት ዓላማውን የማይቀበሉ የአመራር አባላትን መግደሉና ሃያ ያሚሆኑትን ማገርቱ ተገለጸ።
“የተበተኑ የአሸባሪው የሕወሓት ርዝራዦች እስከ አሁን 22 የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አባላትን ገድለዋል፤ 20 የሚሆኑትን አግተዋል” ሲል ያስታወቀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ ነው።
የተበተኑ የአሸባሪው የሕወሓት ርዝራዦች በተለያዩ የትግራይ ክልል አካባቢዎች እስከ አሁን ድረስ ብቻ 22 የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር አባላት መግደላቸውን ፣ ከዚህ በተጨማሪ 20 የጊዜያዊ አስተዳደሩ አባላት መታገታቸውን እና 4 የአስተዳደሩ አባላት ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸው ለሕክምና ሆስፒታል መግባታቸውን ስፍራና የስራ ሃላፊነት ጠቅሶ ይፋ አድርጓል።
“እየታገልኩ ያለሁት ለትግራይ ህዝብ ነው የሚለው አሸባሪው ሕወሓት ይልቁንም የክልሉን ሃብት እያወደመ እንዲሁም በክልሉ መረጋጋትን ለማምጣት የሚሰሩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ አባላትን እየገደለና እያገተ” ነው ሲል መረጃው አስታውቋል።
በትግራይ የሰብአዊ ዕርዳታ በወጉ እንዳይዳረስና በነጻነት እንዳይሰራጭ ህወሃት በየስርቻው እየተሹለከለከ እክል መፍጠሩን፣ ሰላማዊ ዓላማውን የማይደግፉትን አካላት መግደሉን በመጥቀስ የክልሉ ምክትል አስተዳዳሪ መናገራቸው ይታወሳል። ህወሃት ይህን ቢያደርግም የውጭ ሚዲያዎችና የመብት ተቆርቋሪዎች መረጃውን አይጠቀመኡበትም።
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት ውስጥ… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
- “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረውየሚነሳው ጉዳዩ ልብ ሰባሪ ነው፣ ያስቃል፣ ያዝናናል፣ ያስገርማል፣ ያሳዝናል፣ ይቀፋል፣ ያሳፍራል፣ ለማመን ያስቸግራል … አንባቢ ስም ይስጠው። እኔ… Read more: “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረው
- ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!በፖለቲካም ሆነ በአካባቢያዊ አጀንዳ ነፍጥ ያነገቡ እና ጦርነትን አማራጭ አድርገው የሚንቀሳቀሱ ኢ -መደበኛ አደረጃጀቶች ሁሉ የጦር መሳሪያ ፍላጎት… Read more: ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!
- ምን ያክል ተዘጋጅተናል? ጥድፊያ አገር አልባ ለመሆን !! ህጻናቱ ምን አጠፉ?ያለፈውን ግማሽ ምዕተ ዓመት የኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ሥነ መንግሥት ታሪክ በጥሞና የተከታተለ ኢትዮጵያዊ የግዛት አንድነቷን እና የፖለቲካ ነጻነቷን… Read more: ምን ያክል ተዘጋጅተናል? ጥድፊያ አገር አልባ ለመሆን !! ህጻናቱ ምን አጠፉ?
- የደም ግፊት በመለካትና ክትትል በማድረግ የስትሮክ ተጋላጭነትን መቀነስአንድ ሰው የደም ግፊት መጠኑ ከፍተኛ ከሆነ እና በጊዜው ሕክምና ካላደረገ ለከፍተኛ የልብ በሽታና በደም ዝውውር ማነስ ምክንያት… Read more: የደም ግፊት በመለካትና ክትትል በማድረግ የስትሮክ ተጋላጭነትን መቀነስ