በቀጣይ አምስት ዓመታት 500 ሺህ ቤቶችን ለመገንባት አቅዶ እየሰራ ያለው የአዲስ አበባ አስተዳደር የአንድ መቶ ሺህ ቤቶች ግንባታ ለማከናወን ከስምምነት የደረሰ መሆኑንን ይፋ አደረግ።
በዚሁ መረሰረት በአዲስ አበባ ከተማ በአንድ አመት ውስጥ 100 ሺህ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን መገንባት የሚያስችል ስምምነት መፈረሙን የከንቲባ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።ስምምነቱን የፈረሙት በየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤና ፕሮፐርቲ 2000 ደቡብ አፍሪካ ኩባንያ ተወካይ ናቸው።
ለግንባታው 4 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር ወጪ የሚደረግ ሲሆን፥ ሙሉ ወጪው በኩባንያው እንደሚሸፈን ተመልክቷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም ለግንባታ የሚያስፈልገውን መሬት ያቀርባል፡፡
የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ በ30 አመታት ክፍያ ለተጠቃሚዎች የሚተለለፉ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ የተቀናጀ የመንግስትና የግሉ ዘርፍ ትብብር አካል እንደሆነ ተገልጿል፡፡
የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ በአንድ በመቶ አነስተኛ ወለድ ለህብረተሰቡ የሚተላለፉ ሲሆን፥ በቀጣዮቹ አምስት አመታት ውስጥም 500 ሺህ ቤቶች እንደሚገነቡም አስተዳደሩ እግረመነገዱን አስታውቋል።
ለመኖሪያ ቤቶቹ በመሃል ከተማ የመልሶ ማልማት በሚከናወንባቸው እና በአይሲቲ ፓርክ አካባቢ ቦታ መለየቱም በስምምነቱ ወቅት ተነስቷል፡፡
- Ethiopia Working To Secure New Development Bank MembershipThe Ministry of Foreign Affairs disclosed that Ethiopia is working hard to become member of BRICS’… Read more: Ethiopia Working To Secure New Development Bank Membership
- የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”በአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች መመስከራቸውን ቢቢሲ አስታወቀ። ይህ የተገለጸው… Read more: የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”
- በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነውለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ መያዙንna ለዚህም ተግባራዊነት ከሰባት ነጥብ… Read more: በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነው
- አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠአፍሪካ ህብረት የውጭ ምንዛሬ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር እንደሚያዘዋውር ተጠቅሶ በህብረቱ ስም የወጣው ዜና ሃሰት፣ ሆን… Read more: አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠ