በአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች መመስከራቸውን ቢቢሲ አስታወቀ። ይህ የተገለጸው ከአለማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ከሃምሳ ሺህ በላይ ማሻቀቡ ይፋ እየሆነ ባለበት ወቅት ነው።
መንግስት ሰላማዊ ዜጎችን ማህበራዊ ዕረፍት መንሳት አግባብ እንዳልሆነ ጠቅሶ ” መንግስታዊ ሃላፊነትን መወጣት ፍርሃት አይደለም” ቢልም የትግራይ አመራሮች ሂደቱ ከመንግስት ጋር በተደረገ ስምምነት እየተከናወነ እንደሆኢነ አድርገው በተደጋጋሚ እየገለጹ ነው።
ቢቢሲ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች ታጣቂዎቹ በከተማዋ ነዋሪዎች ላይ “ዝርፊያ ፈጽመዋል” ሲሉ ከሰዋል። ቀደም ባሉት ቀናት አብን ባወጣው መግለጫ ” ሰሞኑን በሰሜን ወሎ ራያ አካባቢዎች በተደራጀ መንገድ ወረራ በመፈፀም በብዙ ሽህ የሚቆጠሩ የአካባቢው ኗሪዎችን በማፈናቀል በራያ ባላ፣ አላማጣና ኦፍላ ወረዳዎች እንዲሁም በኮረም ከተማ የሚገኙትን የህዝብ፣ የመንግስትና የሃይማኖት ተቋማትን ንብረት ዘርፏል፤ የአካባቢውን አርሶ አደሮች አዝመራ ዘርፏል በቃጠሎ ጭምር አውድሟል፣ ቤት ለቤት እየገባ ጌጣጌጦችን ሳይቀር ከእናቶች ላይ ቀምቶ ወስዷል፣ የቤት እንስሳቶችን አጓጉዟል፣ ከአርሶ አደሩ ጓዳ የተገኘን እህል ጭኗል ወዘተ። በተመሳሳይ ህወሀት በጎንደር በኩል የወረራና የጥፋት ተግባራትን ለመፈፀም አቅዶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ” ማለቱ አይዘነጋም።
” ታጣቂዎቹ የሰፈሩት በከማው ውስጥ በሚገኙት ስድስት ትምህርት ቤቶች ውስጥ መሆናቸውን የሚናገሩ አንድ ነዋሪ፤ “የትምህር ቤት መጽሐፍት ‘የአማራ ክልል ናቸው’ በሚል ተቀድደዋል” ሲሉ በትግራይ ታጣቂዎች ተፈጽሟል ያሉትን ድርጊት ጠቅሰዋል” ሲል ቢቢሲ ትምህርት መቋረጡን፣ የመንግስት አገልግሎቶች ህክምና ጨምሮ መስተጓጎሉ ጽፏል።
በዚሁ ሳቢያና በከተማዋ ውስጥ በታጣቃዎቹ በሚፈጸሙት ድርጊቶች ምክንያት ነዋሪዎች አሁንም ወደ ቆቦ ከተማ እየሸሹ መሆኑን ነዋሪዎች ገልጸዋል። በቆቦ ከተማ የሚገኙት በአማራ ክልል የተሾሙት የአላማጣ ከተማ ከንቲባ አቶ ኃይሉም የኮረም ከተማ ነዋሪዎች አሁንም ወደ ቆቦ ከተማ እየገቡ መሆኑን ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።
በትግራይ ክልል በኩል የራያ አካባቢ ወረዳ እና ከተማዎችን በስሩ የያዘው የደቡባዊ ትግራይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀፍቱ ኪሮስ፤ በኮረም ከተማ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ገብተዋል ስለመባሉ እና ታጣቂዎቹ ፈጽመዋቸዋል ስለተባሉ ድርጊቶችና በትምህርት ቤቶች ውስጥ ስለምስፈራቸው ቢቢሲ ጠይቋቸው አካባቢው ላይ ስለማ መስፈኑን እንደነገሩት ገልጿል። አያይዘውም “የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ስለመግባታቸው እና በትምህርት ቤቶች ውስጥ ስለ መስረፈራቸው ማረጋገጫ ከመስጠትም ሆነ ከማስተባበል ተቆጥበዋል” ብሏል።
ደጋግመው የፌደራል ፖሊስና መከላከያ በከተሞች ውስጥ እንደሚገኙ የሚናገሩት የትግራይ ሃላፊዎች ጉዳዩን ከመንግስት ጋር በተደረገ ስምምነት መሰረት እንደሚፈጸም ለማስረዳት ሲሞክሩ ይሰማል። በሌላ በኩል ግን መንግስት ለሚመለክታቸው ዓለም አቀፍ ተቋማትና አገራት እንዲሁም ለራሱ ለትህነግ ቀነ ገደብ አስቀምጦ ማስጠንቀቂያ እንደሰጠ እየተነገረና በመግለጫም ተረጋግጧል።
ከ50 ሺህ በላይ ዜጎች መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ይፋ አድርጓል። ድርጅቱ ባለፈው ሰኞ ማምሻ የአካባቢውን ባለሥልጣናት ጠቅሶ እንዳስታወቀው ካለፈው ሚያዝያ አምስት እና ስድስት ጀምሮ በአላማጣ ከተማ ፣ በራያ አላማጣ ዛታ እና ኦፍላ በተካሄደው ግጭት የተፈናቀሉት ሰዎች ቁጥር ከ50 ሺህ በላይ ሆኗል። ከተፈናቃዮቹ መካከል በሺህዎች የሚቆጠሩ ሴቶችና ህጻናት መኖራቸውን ድርጅቱ አመልክቷል። በሕይወት ለመቆየት ሰፊ ሰብዓዊ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸውም አሳስቧል። ድርጅቱ አያይዞም እነዚህ ተፈናቃዮች የሚገኙባቸው ሰብዓዊ ይዞታም አሳሳቢ እነደሆነ አስታውቋል። እውነታው ይህ ቢሆንም የትግራይ ሃላፊዎች ” ሰላም ሰፍኗል” በሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
የጀርመን ድምጽ ያነጋገራቸው እንዳሉት አሁን ላይ በከፍተኛ ችግር ላይ ናቸው። በተጠለሉበት የስደት ስፍራ ድጋፍ አላገኙም። ልጆች በከፋ ስቃይ ላይ ናቸው። ዘገባው እንዲህ ይላል።
ግጭቱ እስከተከሰተበት ጊዜ ድረስ የአላማጣ ከንቲባ ሆነው የቆዩት የራያ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ኃይሉ አበራ፤ ኅብረተሰቡ ከስድስት ወረዳዎች መፈናቀሉን ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል። ለተፈናቃዩ ኅብረተሰብ እህል ማቅረብ ባለመቻሉ እራሱ የከተማው አስተዳደር ለተወሰኑ ቀናት ዳቦ እየገዛ ለመመገብ መሞከሩንም ተናግረዋል።ሆኖም ችግሩ ከአቅም በላይ በመሆኑ እና፤ተፈናቃዮቹን በመጠለያ ጣቢያ ማስቀመጥ ለተለያዩ ተላላፊ በሽታዎች እና ለከፋ ማህበራዊ ቀውስ ሊያጋልጥ ይችላል በሚል ወደ ቀያቸው ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። የተፈናቃዮች የድረሱልን ጥሪ
በአማራና ትግራይ የይገባኛል ጥያቄ በሚነሳባቸው አዋሳኝ አካባቢዎች የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ፤ በአካባቢው የሚደርሰው ጉዳት እንዳሳሰበው ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እየገለፀ ሲሆን፤ ከነዚህም መካከል በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ ፣የጃፓን፣ የብሪታንያ እና የፈረንሳይ ኤምባሲዎች ችግሩ በውይይት እንዲፈታና ለሰላማዊ ሰዎችም ጥበቃ እንዲደረግ ጥሪ ማቅረባቸው ይታወሳል።
የአማራ ክልል መንግስት ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ «ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ለአራተኛ ዙር ሕዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል» ሲል ከሶ አካባቢውን ለቆ ካልወጣ ህዝቡን ከጥቃት ለመከላከልና ክልሉንም ከጥፋት ለማዳን ይገደዳል ሲል አስታውቆ ነበር።
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጀኔራል ታደሰ ወረደ ደግሞ «በኃይል የተያዙ የትግራይ አካባቢዎች» ያሏቸውን ቦታዎች በኃይል ለማስመለስ እንደማይፈልጉ ሆኖም ችግሮቹ ከፌደራል መንግሥት ጋር በመነጋገርና በመግባባት የሚፈቱ እንደሚሆን ባለፈው ሳምንት ገልፀዋል ይላል የጀርመን ድምጽ ጥንቅር።
ቢቢሲ ዜናውን አስታኮ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ ማሐማት ባወጡት መግለጫ አዲስ እየታየ ያለውን የነዋሪዎች መፈናቀልን ለማስቆም ውጥረት ባለባቸው አካባቢዎች ያሉ ሁሉም ወገኖች “በአስቸኳይ ጠላትነትን እንዲያስወግዱ እና የሰላማዊ ሰዎችን ደኅንነት እንዲያረጋግጡ” ጥሪ ማቅረባቸውን አመልክቷል።
ሊቀመንበሩ አክለውም በፌደራል መንግሥቱ እና በህወሓት መካከል ከሁለት ዓመት ገደማ በፊት ግጭትን በዘላቂነት ለማስወገድ ደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ላይ የተደረሰው ስምምነት ተከብሮ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ እንዲሆን ጠይቀዋል።
አክለውም በስምምነቱ ላይ እንደተመለከተው ይገባኛል የሚነሳባቸውን አካባቢዎች ጉዳይ በዘላቂነት ምላሽ ለመስጠት የሚያስችለውን ፖለቲካዊ ውይይት እንዲጀመር ጥሪ አቅርበዋል።
በተመሳሳይ በትግራይ ክልል የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ ወደ አማራ ክልል እንዲጠቃለሉ በተደረጉ የአላማጣ ከተማ እና ራያ ወረዳዎች እንደ አዲስ የተቀሰቀውን ግጭት ተከትሎ በአዲስ አበባ መቀመጫቸውን ያደረጉ የካናዳ፣ የፈረንሳይ፣ የጀርመን፣ የጣሊያን፣ የጃፓን፣ የዩናይትድ ኪንግደም እና የአሜሪካ ኤምባሲዎች ውጥረት እንዲረግብ ሰሞኑን ጠይቀዋል።
ኤምባሲዎቹ ሁሉም አካላት ትጥቅ በመፍታት እና መልሶ ከማኅበረሰቡ ጋር ለማዋሃድ እንዲሁም የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ መኖሪያ ቀያቸው ለመመለስ በሚደረጉ ጥረቶች ላይ አጽንኦት ተሰጥቶ እንዲሠራ አሳስበዋል።