ፖሊስ ወደ ስፍራው ሲደርስ ተጠርጣሪዋ ሰራተኛ እንደሌላት በመናገር ልትደብቃት ብትሞክርም ሰራተኛዋ ግን አልጋ ውስጥ ሆና ስትጮኽ ፖሊስ በመስማቱ ከስቃይ ሊያድናት እና አሰሪዋንም በቁጥጥር ስር ሊያውላት መቻሉን አቶ ዮሐንስ ገልፀዋል።
በቦሌ ክፍለ ከተማ የቤት ሰራተኛዋን በአሰቃቂ ሁኔታ ከ1 ዓመት በላይ ከቤት እንዳትወጣና የፀሃይ ብርሃን እንዳታገኝ በማድረግ፣ ምግብ በመከልከል ከፍተኛ ድብደባ ስትፈፅም የነበረች ተጠርጣሪን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ ተገለፀ።
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በክፍለ ከተማው ወረዳ 8 ሲ.ኤም.ሲ አልታድ መንደር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡ የቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የሴቶችና ህፃናት ወንጀል ምርመራ ማስተባበሪያ ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር ኤርሚያስ ጋቸኖ እንደገለፁት አንዲት ግለሰብ በቤት ሰራተኝነት የቀጠረቻትን የ20 ዓመት ወጣት በተደጋጋሚ በመደብደብ፣ ምግብ በመከልከል፣ በር በመቆለፍ ከቤት እንዳትወጣ እና የፀሃይ ብርሃን እንዳታይ እያደረገች ስትበድላት ቆይታ የቤቱ አከራይ ለፖሊስ በሰጡት ጥቆማ በቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተጣራባት ይገኛል።
የግል ተበዳይ የሆነችው ወጣት ጥሩአለም ደጉ በቤት ሰራተኝነት ከተቀጠረች ጊዜ ጀምሮ ለ1 አመት ከ2 ወር ያህል ከባድ የሆነ ስቃይ ሲደርስባት እንደነበር በመግለፅ ፖሊስ ደርሶ ህይወቷን እንዲያተርፍላት ለቤቱ አከራይ በአጋጣሚ ባገኘችው የመስኮት ቀዳዳ ወረቀት ፅፋ መስጠቷን ተናግራለች ።
የቤቱ አከራይ አቶ ዮሐንስ ኃ/ጊዮርጊስ በበኩላቸው ሰራተኛዋን የተቀጠረች ቀን ብቻ ማየታቸውንና በተደጋጋሚ ያስቀጠራትን ደላላ ስለ ልጅቷ ጉዳይ መጠየቃቸውን ተናግረው በወረቀት ተፅፎ በመስኮት የተወረወረላቸውን መልዕክት ካገኙ በኋላ ለአቅራቢያቸው ፖሊስ ጣቢያ መጠቆማቸውን ገልፀዋል፡፡
ፖሊስ ወደ ስፍራው ሲደርስ ተጠርጣሪዋ ሰራተኛ እንደሌላት በመናገር ልትደብቃት ብትሞክርም ሰራተኛዋ ግን አልጋ ውስጥ ሆና ስትጮኽ ፖሊስ በመስማቱ ከስቃይ ሊያድናት እና አሰሪዋንም በቁጥጥር ስር ሊያውላት መቻሉን አቶ ዮሐንስ ገልፀዋል።
ህብረተሰቡ በአካባቢው የሚፈፀሙ የወንጀል ድርጊቶችን ለፀጥታ አካላት ሊጠቁምና በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን ለመከላከል አካባቢውን በንቃት ሊመለከት እንደሚገባ ረዳት ኢንስፔክተር ኤርሚያስ ጋቸኖ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ ዘገባ፡- ምክትል ሳጅን አዳነ ደስታ
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን ለጎን የትግራይ ከፍተኛ ባለስልጣናትና የዞን አስተዳዳሪዎች የተባሉ ሁለት ዓይነት መረጃዎች እየሰጡ ነው። መንግስት ግን ስምምነት መኖሩን ዘርዝሮ እነሱ በሚሉት መልኩ ባለመሆኑ ” ትዕግስት ፍርሃቻ አይደለም” እያለ ነው።ከትናንት በስቲያ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ግንባታ ማስተባበሪያ እና… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች ዜና የሚያቀብሉና እነሱኑ የሚከተሉ ስምምነቱ መክሸፉንና መንግስት ውሉን እንደተወው፣ የሶማሌ ማንግስትም መንግስት በአደባባይ ስምምነቱን ማቆሙን እንዲያውጅ እንደሚያደርግ አስታውቀው እንደነበር ይታወሳል። ሌሎች አገራት ከሶማሌላንድ ጋር መሰል ስምምነትን ሲያደርጉ ዝምታን የመረጡ፣ የግብጽን፣ የኤርትራንና የሶማሌን የተቀነባበረ ሴራ ተከትለው ኢትዮጵያ… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን ዋስትና አፀና። ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎቹ ከሀገር እንዳይወጡ እግድ እንዲጣል ትዕዛዝ ሰጥቷል። ተጠርጣሪዎቹ የቀድሞ የህዝብ ትራንስፖርት የተሽከርካሪ ዘርፍ ኃላፊና የትራንስፖር ሎጂስቲክ ሚኒስትር አማካሪ የነበሩት ከድልማግስት ኢብራሂም፣ የትራንስፖርት ማህበራት አመራርና አባል ታምራት በየነ፣ ጌትነት በየነ እንዲሁም የመናኸሪያ የትራንስፖርት ስምሪት ኃላፊዎች… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት ውስጥ የሚኖሩ ዜጎቹን መልሶ ለመቀበል ያሳየው ተባባሪነት አናሳ መሆኑን ካውንስሉ ባደረገው ግምገማ ስለተገነዘበ” ነው። “የኢትዮጵያ ባለሥልጣኖች ዜጎችን መልሶ ለመውሰድ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ አልሰጡም” በማለት የካውንስሉ መግለጫው ያብራራል። የአስቸኳይ ጊዜ የጉዞ ሰነዶች በመስጠት እንዲሁም በፍቃድ እና ያለ ፈቃድም የሚደረግ… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
- “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረውየሚነሳው ጉዳዩ ልብ ሰባሪ ነው፣ ያስቃል፣ ያዝናናል፣ ያስገርማል፣ ያሳዝናል፣ ይቀፋል፣ ያሳፍራል፣ ለማመን ያስቸግራል … አንባቢ ስም ይስጠው። እኔ ስጽፈው ግን በሃፍረት ስሜት ነው። ያፈርኩት ደግሞ በደርስንበት የሞራል ውድቀት ነው። እንደ ማህበረሰብ ይሁን እንደ ቡድን በውል ባላውቅም ግን ወድቀናል። የወደቅንበት የሃፍረታችን ገደል ርቀቱ እንዲሁ በቀላሉ የሚወጣበትም አይመስልም። ሃፍረቴና ተስፋዬ በኩል ደረጃ እየተናነቁኝ ስለ አብሮ አደጎቼ ጻፍኩ።… Read more: “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረው