አሜሪካ በትግራይ ክልል ያለው ችግር እንዲረጋጋ ፍላጎት እንደሌላትና በተቃራኒ ችግሩ እንዲባባስ እያደረገች ነው ስትል ኤርትራ ወቀሳ መሰንዘሯ ተሰምቷል፡፡
የኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ትላንት ሰኞ በላከው ደብዳቤ ደብዳቤ እንደገለጸው የባይደን አስተዳደር በትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ እንዳይረጋጋ ፍላጎት እንደሌለው መግለጹ ተዘግቧል፡፡
ለዚህም አሜሪካ ላለፉት 20 ዓመታት ለአሸባሪው ህወሃት ቡድን ስታደርግ የነበረውን ድጋፍ በማስታወስ ለችግሩ መከሰት ኤርትራን ተጠያቂ ማድረግም መሰረት የሌለው እንደሆነ ገልጿል፡፡የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳልህ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት የጻፉት ደብዳቤ አሜሪካ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ላይ በምታደርገው ጣልቃ ገብነትና እየፈጠረች ባለችው ያልተገባ ጫና ተጨማሪ ችግር እንዲፈጠር እያደረገች መሆኑንና ችግሩ እንዳይቀረፍ እንቅፋት እየሆነች እንደሆነ የሚገልጽ ይዘት ያለው መሆኑን በዘገባው ተገልጿል፡፡
በተጨማሪም ኤርትራ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በላከችው ደብዳቤ ላይ አሜሪካ የሽብር ቡድኑ ቀደሞ ወደ ነበረበት ስልጣን ለመመለስ ፍላጎት እንዳላትም መግለጹ ተነግሯል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ኦስማን ሳልህ የህወሃት ቡድን አሁን ሀገሪቱን እያስተዳደረ ያለውን የዶ/ር አብይ አስተዳደርን በዓለም አቀፉ ማህበረሰቡ ዘንድ አሉታዊ ገጽታ እንዲይዝ የሚያደርጉ የተዛቡ መረጃዎችን በማሰራጨት መወጠሩን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትም ፍትህን ማረጋገጥ የሚያስችሉ እርምጃዎች መውሰድ ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡
ሚኒስትሩ አክለውም የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ሰሞኑን በኢትዮጵያና በኤርትራ ባለስልጣናት እና በወታደራዊ ሀላፊዎች ላይ የጣለውን የጉዞ ዕገዳ በተመለከተም ተገቢነት የጎደለው እና በሀገራት የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ የመግባት አንዱ ማሳያ ሲሉ መተቸታቸውን አልጀዚራ በዘገባው አስነብቧል፡፡
- Ethiopia Working To Secure New Development Bank MembershipThe Ministry of Foreign Affairs disclosed that Ethiopia is working hard to become member of BRICS’ New Development Bank.… Read more: Ethiopia Working To Secure New Development Bank Membership
- የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”በአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች መመስከራቸውን ቢቢሲ አስታወቀ። ይህ የተገለጸው ከአለማጣ እና አካባቢው… Read more: የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃፍትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”
- በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነውለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ መያዙንna ለዚህም ተግባራዊነት ከሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊየን በላይ… Read more: በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነው
- አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠአፍሪካ ህብረት የውጭ ምንዛሬ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር እንደሚያዘዋውር ተጠቅሶ በህብረቱ ስም የወጣው ዜና ሃሰት፣ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ መሆኑን… Read more: አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን አረጋግጠ
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ። አሁን… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች