አቶ ደመቀ መኮንን ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሃላፊነታቸው በተጨማሪ ደርበው እየሰሩ ላሉበት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቦታ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሙስጣፌ መታጨታቸው ተሰማ። ክልሉና በውጭ አገር ያሉ የክልሉ ተወላጆች በዜናው ደስተኛ አይደሉም።
የአብዲሌ ወንበር ላይ ከተቀመጡ ጀምሮ እጅግ በሚገርም ሁኔታ በመላው አገሪቱ ተቀባይነት ያገኙት ሙስጣፌ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርነት የታጩት ገዢው ፓርቲ ብልጽግና በምርጫው ካሸነፈ አዲስ በሚዋቀረው ካቢኔ የሚካተቱ እንዲሆን ታስቦ ነው።
በሚመሩት ክልል ሁሉም ብሄረሰቦች እኩል ሆነው የሚስተናገዱበትን፣ ቋንቋውን ከቻሉ በሃላፊነት የሚመደቡበትንና ልዩነት የሌለበትን አሰራር በማስፈን ሰላም ያወረዱት ሙስጣፌ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እንዲሆን መታጨታቸውን አስመልክቶ የክልሉን ተወላጅ ዲያስፖራ አባላትን አናገረን ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
የሜኖሶታ ነዋሪ የሆኑ የሶማሌ ተወላጅ ” ዜናውን ሰምተናል፤ ደስተኛ አይደለንም” ብለዋል። በሙስጣፌ ሹመት ሳይሆን ክልሉ ላይ የጀመሩትን ተግባር እንዲያጠናክሩ ከመመኘት አንጻር ባሉበት እንዲቀጥሉ ምኞታቸው እንደሆነም አስታውቀዋል። ክልሉ አካባቢም ተመሳሳይ እምነት እንዳለ ለማወቅ ችለናል።
በሌላ ዜና የሜኖሶታ ነዋሪ የሶማሌ ተወላጆች አሁን አሜሪካ ኢትዮጵያ ላይ የያዝቸውን አቋም እንዲላዘብ እየሰሩ መሆናቸው ታውቋል። ሰፊ የሶማሌና የኦሮሞ ማህበረሰብ ባለበት ሚኖሶታ የሶማሌ ድምጽና ተጽዕኖ ከፍተኛ በመሆኑ በአካባቢው ያሉትን ሴናተር ማሳመናቸውም ታውቋል። ትናት ወደ ሜኖሶታ ያቀናው የክልሉ ሉዑል ቡድን ከባለስልታኑ ጋር እንዲገናኝ መመቻቸቱንም ጠቁመውናል።
ሙስጣፊ በትህነግና በትህነግ ደጋፊዎች ዘንድ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ቀጥለው የሚጠሉ፣ በመላው አገሪቱ ደግሞ ተቀባይነትን ያገኙ የለውጡ ቱርፋት የሆኑ አዲስ መሪ መሆናቸው ይታወቃል።
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
- “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረውየሚነሳው ጉዳዩ ልብ ሰባሪ ነው፣ ያስቃል፣ ያዝናናል፣ ያስገርማል፣ ያሳዝናል፣ ይቀፋል፣ ያሳፍራል፣ ለማመን ያስቸግራል … አንባቢ ስም ይስጠው።… Read more: “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረው