በፎቶው ላይ የሚታዩት የውሃ፣ መስኖ እና ኢንርጂ ሚንስትሩ ስለሺ በቀለ (ዶ/ር፣ ኢንጂነር፣ የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፣የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣የትራንስፖርት ሚንስትሯ ዳግማዊት ሞገስ፣ዛዲግ አብርሀ፣ የብሔራዊ ባንክ ገዢው ዶ/ር ይናገር ደሴ፣ ፕ/ር ሂሩት ወ/ማርያም፣ የአገር አቀፍ ምዘና እና ፈተናዎች ኤጀንሲ ዳይሬክተር ዲላሞ ኦቶሬ ናቸው።
በዘንድሮው ምርጫ ብልፅግና ፓርቲ ከ436 መቀመጫዎች ውስጥ 410 ያሸነፈ ሲሆን ለቀጣዩ አምስት አመታትም መንግሥት መመስረት የሚያስችለውን ወንበር አግኝቷል።
ለዘመናት የአገሪቱ ዋነኛ የፖለቲካ ማዕከል ሆና በቆየችው አዲስ አበባ በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ከተማዋ ላይ ባተኮረ መልኩ ፖሊሲዎችን ሲቀርፁና ሲንቀሳቀሱ ይታያሉ።
በዘንድሮው ምርጫ ብዙ ትኩረት በነበረባት አዲስ አበባ የተመዘገቡ መራጮች ቁጥር 1,819,343 ሲሆን ከዚህም ውስጥ 99ኛው በመቶ ድምፅ ሰጥቷል።
አዲስ አበባ ከተማ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 23 መቀመጫዎች ያሏት ሲሆን ገዢው ፓርቲ ብልፅግና 22 መቀመጫዎችን ሲያሸንፍ በግል የተወዳደሩትና የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት መቀመጫ አግኝተዋል።
ለመሆኑ በቀጣዮቹ አምስት አመታት አዲስ አበባን በፓርላማ የሚወክሏት እነማን ናቸው?
- ምርጫ ክልል 1- ፕ/ር ኢያሱ ኤልያስ
- ምርጫ ክልል 2 ብርሃነ መስቀል ጠና
- ምርጫ ክልል 3 የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ
- ምርጫ ክልል 4 ሙሉ ይርጋ
- ምርጫ ክልል 5 ያስሚ ወህቢ
- ምርጫ ክልል 6 ዶክተር ወንድሙ ተክሌ
- ምርጫ ክልል 7 በሕዳሴ ግድብ ዙሪያ የኢትዮጵያ አቋም ለአረቡ ዓለም በማንጸባረቅ የሚታወቁት መሐመድ ከማል አሊ አል-አሩሲ
- ምርጫ ክልል 8 የትራንስፖርት ሚንስትሯ ዳግማዊት ሞገስ
- ምርጫ ክልል 10 ዶ/ር ቤተልሄም ላቀው
- ምርጫ ክልል 11 ፕ/ር ሂሩት ወ/ማርያም፣
- ምርጫ ክልል 12 እና 13 ዕጩ ሲሆኑ ዶ/ር ስንታየሁ ወ/ሚካኤል
- ምርጫ ክልል 15 ህይወት ሞሲሳ
- ምርጫ ክልል 16 ሰሃርላ አብዱላሂ
- ምርጫ ክልል 17 የውሃ፣ መስኖ እና ኢንርጂ ሚንስትሩ ስለሺ በቀለ (ዶ/ር፣ ኢንጂነር)፣
- ምርጫ ክልል 18 ዛዲግ አብርሀ
- ምርጫ ክልል 19 ዶ/ር ትዕግስት ውሂብ
- ምርጫ ክልል 20 የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ
- ምርጫ ክልል 21 እና 22 የብሔራዊ ባንክ ገዢው ዶ/ር ይናገር ደሴ
- ምርጫ ክልል 23 የአገር አቀፍ ምዘና እና ፈተናዎች ኤጀንሲ ዳይሬክተር ዲላሞ ኦቶሬ
- ምርጫ ክልል 24 ዶ/ር ከይረዲን ተዘራ
- ምርጫ ክልል 25 ዶ/ር ቶፊቅ አብዱላሂ
- ምርጫ ክልል 26 እንዳልካቸው ሌሊሳ
- ምርጫ ክልል 28 በግል ተወዳዳሪነት የቀረቡትና የጠቅላይ ሚኒሰትሩ አማካሪ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ናቸው።
የክልል ምክር ቤቶችን በምንመለከትበት ወቅት ብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባን ምክር ቤት ሁሉንም 138 መቀመጫዎችን አሸንፏል።
ምርጫ 2013 በጨረፍታ
- 37,408,600 መራጮች ተመዝግበዋል ከዚህ ውስጥ 20,317,472 ወንዶችና 17, 091, 128 ሴቶች ናቸው
- 47 ፓርቲዎች 8,209 እጩዎችን አቅርበዋል 125 የግል ተወዳዳሪዎችም
- 634 የምርጫ ክልሎችና 49, 407 የምርጫ ጣቢያዎች
- 52,700 የምርጫ አስፈጻሚዎች፤ በእያንዳንዱ የምርጫ ጣቢያ 5 አስፈጻሚና 1 የኮቪድ-19 ቁጥጥር ባለሙያ
- ሰኔ 14/2013 ዓ.ም በተደረገው ምርጫ ለ445 የፓርላማ መቀመጫዎች ድምጽ ተሰጥቷል
- ጳጉሜ 01/2013 ደግሞ ለቀሪዎቹ 64 ወንበሮች ድምጽ ይሰጣል
ምስጋና ፎቶና ዘገባ ቢቢሲ
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን ዋስትና አፀና።… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት ውስጥ የሚኖሩ… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
- “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረውየሚነሳው ጉዳዩ ልብ ሰባሪ ነው፣ ያስቃል፣ ያዝናናል፣ ያስገርማል፣ ያሳዝናል፣ ይቀፋል፣ ያሳፍራል፣ ለማመን ያስቸግራል … አንባቢ ስም ይስጠው። እኔ ስጽፈው… Read more: “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረው