በኢትዮጵያዊያን አቆጣጠር የህዳሴው ግድብ ዛሬ ለሌት ሲሞላ ” ኢትዮጵያ ኒኩሌር ታጠቀች” ማለት እንደሆነ ባለሙያዎች አስታወቁ። ሲያብራሩም የህዳሴውን ግድብ መሙላት ማለት ግድቡን ከማንኛውም ክፉ ሙከራ መታደግ እንደማለት ነው።
“በኢትዮጵያዊያን ደም፣ አጥንትና ላብ የተሰራ ነው” ሲሉ ድየውሃና መስኖ ሚኒስትሩ ዶክተር ስለሺ የገለጹት የህዳሴው ግድብ የኮንክሪት ሙሌት ስራ ተገባዷል። ወይም እንደተገባደደ ይታመናል። በዚሁ ሂሳብ መሰረት ከፍታው ከባህር ወለል በላይ 574 ሜትር ሆኗል። ዶክተር ስለሺ በተደጋጋሚ እንደተናገሩት የውሃው ሙሌት ሲጠናቀቅ በሁለት ተርባይን የኤሌክትሪክ ሃይል ለማምረት የተያዘው ዕቅድ የሚሳካ ነው።
የሁለተኛውን ዙር የውሃ ሙሌት አስመለክቶ ግብግብ ፈጥራ የነበረችው ግብጽ የውሃው ሙሌት ጫፍ መድረሱንና ምንም ማድርተግ የማይቻልበት ደረጃ መድረሱን ስትረዳ አልሲሲ “ኢትዮጵያን በልማት ማገዝ እንፈልጋለን” ማለታቸውን ያስታወሱ ባለሙያዎች እንዳሉት ካሁን በሁዋላ የህዳሴው ግድብ ጥበቃ አያስፈልገውም።
ግብጽ ግድቡን ብትመታ ሽቅብ ወደላይ ሳይሆን ወደታች ሲወርድ ሱዳንና ግብጽን ተረት እንደሚያደርጋቸው በሂሳብ የሚያስረዱ እንዳሉት፣ ግብጽ ካሁን በሁዋላ ማተረማመሷን ታስቀጥል ካልሆነ በቀር ህዳሴውን ግድብ አስመልክቶ አንዳችም ክፋት ማሰብ አትችልም።
ነገ የወሃው ሙሌቱ ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያዊያን በይፋ ” ኒኩሌር ታጠቁ እንደማለት ነው” ሲሉ የተናገሩትም በዚሁ መነሻ መሆኑንን አመልክተዋል። “ምርጫ ካካሄደች ኢትዮጵያ ትፈርሳለች” ሲባል የተሳካ ምርጫ ማካሄዷን፣ የህዳሴው ግድብ ሁለተኛ ሙሌት መሳካቱን አንድ ላይ አዳምረው ለኢትዮጵያዊያን ይህ ታላቅ የድል ዜና እንደሆነ እየተገለጸ ነው።
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች በስሟ የሚገዘቱት እንጀራዋን ለመብላት እንጂ መከራዋን ለመካፈል… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤ ወንጌላዊ መኾን መልካም ነው፣ ወንጀለኛ መኾን ግን ሐጥያት… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣ እንዲሁም ትኩረቴ በቀላሉ ይከፋፈል ነበር። ሐኪሜ የብረት ማዕድን… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን ለጎን የትግራይ ከፍተኛ ባለስልጣናትና የዞን አስተዳዳሪዎች… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች ዜና የሚያቀብሉና እነሱኑ የሚከተሉ ስምምነቱ መክሸፉንና… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት