በኤርትራና በኢትዮጵያ የተፈጸመው የዕርቅ ሂደትን ሰላም መምጣቱ ያላስደሰታቸው አሜሪካ እና የቀድሞ ቅኝ ገዢዎች (አውሮፓ ሕብረት) በህዋሃት በኩል ኢትዮጵያ ውስጥ ሁከትና ብጥብጥ እየፈጠሩ መሆኑን እያየነው ነው። ቢሆንላቸው ጠ/ሚሩን ለማስወገድ ወይም አደጋ ላይ ለመጣል የሚችሉትን ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማይሉ እናውቃለን። አፍሪካ ውስጥ በተለይ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰላም እና አንድነት እንዲጠናከር አይፈለግም። በአፍሪካ ምድር የቅኝ አገዛዝ ዘመን ካበቃ በኋላ ሃያ ዘጠኝ ሰላም ወዳድና ለሃገራቸው ህዝብ የቆሙ መሪዎች በአሜሪካና ሌሎች ውጪ ሃይሎች ጣልቃ ገብነት ተገድለዋል።
ልጅ ግሩም ( ፒኤችዲ)
እርቅ፣ ሰላም እና ትብብር የሚል ሀሳብ ስለፈለገ ብቻ ነው። ግብፅን እንደ ምሳሌ እንመልከት፡-ግብፃውያን ከእስራኤል ጋር አራት ጊዜ ታላላቅ ጦርነቶችን አካሂደዋል፡፡ እስከ መጀመሪያው የግብፅ አብዮት መሪ ጋማል አብድል ናስር አስተዳደር ድረስ ከእስራኤል ጋር ሦስት ጦርነቶች ተካሂደዋል፡፡
ፕሬዝዳንት አንዋር ሳዳትንም አራተኛውን ጦርነት ተሸንፈው በኋላ ግን ፊታቸውን ወደ ሰላም አዞሩ፡፡ የዛሬ 40 ዓመት ገደማ በዘመኑ ብዙዎችን ያስገረመ ያስደነቀም ያልተጠበቀም ነገር አደረጉ፡፡ የሰላም እና እርቅ ንግግር ለማድረግ ወደ እስራኤል አቀኑ፡፡
ከዘመኑ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ሜኒያሂም ቤጊን ጋር ፊት ለፊት ተገናኝተው በመነጋገር የመጀመሪያው አረብ ሆኑ። በጊዜው ለፍልስጤማውያን ተቆርቋሪዎች ነን ይሉ የነበሩ የአረብ አገሮችና ሌሎች ሳዳትን በከሃዲነት አብጠለጠሏቸው፡፡
ሰላምን መምረጣቸው የተቀረውን ዓለም አድናቆት አተረፉ፣ ተወደሱ፣ ተሞገሱበት፡፡ እስራኤል በስድስቱ ቀን ጦርነት ከግብፅ የነጠቀችውንና በኋላም ያስፋፋችውን የሲናይ ግዛት ለግብፅ መለሰች። ፕሬዝዳንት ሳዳት የኖቤል የሰላም ሽልማት (1978) አሸናፊ ሆኑ፡፡ ከሶስት በኋላ ዓመታት በኋላ (October 6, 1981) በካይሮ በአንድ የሠልፍ ስነ-ስርዓት ላይ በህዝብ ፊት መድረክ ላይ ተቀምጠው እያሉ ተተኩሶባቸው ተገደሉ። በተመሳሳይ ስሌት ሰኔ 16 ቀን በመስቀል አደባባይ የተከሰተውን እናስታውሳለን።
በኤርትራና በኢትዮጵያ የተፈጸመው የዕርቅ ሂደትን ሰላም መምጣቱ ያላስደሰታቸው አሜሪካ እና የቀድሞ ቅኝ ገዢዎች (አውሮፓ ሕብረት) በህዋሃት በኩል ኢትዮጵያ ውስጥ ሁከትና ብጥብጥ እየፈጠሩ መሆኑን እያየነው ነው። ቢሆንላቸው ጠ/ሚሩን ለማስወገድ ወይም አደጋ ላይ ለመጣል የሚችሉትን ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማይሉ እናውቃለን። አፍሪካ ውስጥ በተለይ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰላም እና አንድነት እንዲጠናከር አይፈለግም። በአፍሪካ ምድር የቅኝ አገዛዝ ዘመን ካበቃ በኋላ ሃያ ዘጠኝ ሰላም ወዳድና ለሃገራቸው ህዝብ የቆሙ መሪዎች በአሜሪካና ሌሎች ውጪ ሃይሎች ጣልቃ ገብነት ተገድለዋል።
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን ለጎን የትግራይ ከፍተኛ ባለስልጣናትና የዞን… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች ዜና የሚያቀብሉና እነሱኑ የሚከተሉ ስምምነቱ… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን ዋስትና አፀና። ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎቹ ከሀገር እንዳይወጡ… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት ውስጥ የሚኖሩ ዜጎቹን መልሶ ለመቀበል ያሳየው ተባባሪነት… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
- “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረውየሚነሳው ጉዳዩ ልብ ሰባሪ ነው፣ ያስቃል፣ ያዝናናል፣ ያስገርማል፣ ያሳዝናል፣ ይቀፋል፣ ያሳፍራል፣ ለማመን ያስቸግራል … አንባቢ ስም ይስጠው። እኔ ስጽፈው ግን በሃፍረት ስሜት ነው። ያፈርኩት… Read more: “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረው