በትግራይ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ሲማሩ የነበሩ ተማሪዎች አፋር ክልል ሰመራ ከተማ መግባት መጀመራቸው አል ዐይን አማርኛ ያነጋገራቸው የሰመራ የከተማዋ ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡የተማሪዎች ወላጆች ከሰሞኑ ልጆቻቸው ትግራይ ክልል ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲመለሱ ጥያቄ ሲያቀርቡ ቆይተዋል፡፡
የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከትግራይ ክልል መውጣት ከጀመረ እና የተናጠል ተኩስ አቁም ከታወጀ በኋላ ትግራይ ክልል ባሉ ዮኒቨርሲቲዎች ልጆች ያሏቸውን ወላጆች ሲያሳስብ ቆይቷል፡፡
አሁን ላይ በትግራይ ክልል ከሚማሩ ተማሪዎች መካከል 325 የሚሆኑት በሰመራ ዩኒቨርሲቲ አቀባበል እንደተደረገላቸው ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የሰመራ ከተማ የሥራ ኃላፊ ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል፡፡
ዛሬ ሰመራ የገቡት ተማሪዎች ወደ የቤተሰቦቻቸው እየተሸኙ መሆኑ የስራ ኃለፊው ተናግረዋል፡፡በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ልጆች ያሏቸው ወላጆች፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) ልጆቻቸው የሚመለሱበትን መንገድ እንዲያመቻችላቸው ከሰሞኑ በሰልፍ ጠይቀው ነበር፡፡ትግራይ ክልል ባለው ግጭት ሳቢያ ስጋት ያደረባቸው ወላጆች ከተመድ በተጨማሪ፤ መንግስት በትግራይ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ባሉ በተማሪዎቹ ዙሪያ እልባት እንዲሰጣቸው በተደጋጋሚ ሲጠይቁ ነበር፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ት/ምሚኒስቴር በወቅቱ “ከየዩኒቨርስቲዎቹ አመራሮች እና ከዓለም አቀፍ ተራድኦ ተቋማት ጋር በመሆን ጉዳዩን እየሰራበት ይገኛል፡፡ በተደረገው ጥረትም የዩኒቨርቲዎችን አመራር ለማግኘት የተቻለ ሲሆን ተማሪዎች በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኙና የሁለተኛ መንፈቅ ዓመት ፈተና ለመውሰድ በዝግጅት ላይ ያሉም እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል” ሲል ለወላጆች ጥያቄ መልስ መስጠቱ ይታወሳል፡፡Via #alainamharic
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ።… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
- “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረውየሚነሳው ጉዳዩ ልብ ሰባሪ ነው፣ ያስቃል፣ ያዝናናል፣ ያስገርማል፣ ያሳዝናል፣ ይቀፋል፣ ያሳፍራል፣ ለማመን ያስቸግራል … አንባቢ ስም… Read more: “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረው