አዲስ አበባ በሁለት ሳምንት ለመግባት የሚያግደው አንዳችም ሃይል እንደሌለ በይፋ ያስታወቀውና በቃል አቀባዩ ጌታቸው አማካይነት ትናንት ጎንደርና ወልቃይት በአሸባሪው ትህነግ እጅ መውደቁን ያወጀው ቡድን ያስቀመጠውን ቅድመ ሁኔታ ትቶ ድርድር እንደሚፈልግ ማስታወቁ ተሰማ። ለዚሁ ተግባር አዲስ አበባ የገቡ አሜሪካዊ አማላጆች መኖራቸውን ታውቋል።
ቀደም ሲል ስምንት ቅደመ ሁኔታዎችን አስቀምጦ የነበረው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ” ድል በድል ሆኛለሁ” እያለ ባለበት ሰዓት ለምንና እንዴት ለተኩስ አቁም አስቀምጦት የነበረውን ቅድመ ሁኔታ ለማንሳት እንደወሰነ የታወቀ ነገር የለም።
” ገና ከአማራ ጋር የምናወራርደው ሂሳብ አለ” በሚልና የማዕከላዊ መንግስቱን ለመጣል በኦሮሞ ጽንፈኞች አማካይነት የተለያየ ሙከራ ሲያደርግ የነበረው ትህነግ አቋሙን ቀይሮ መደራደር እንደሚፈልግ ሁለት የአሜሪካ መልዕከተኞች አዲስ አበባ መግባታቸውን የአዲስ አበባ ተባባሪያችን አመልክቷል።
ወልቃይትና ጎንደር እጅቻእው መግባቱን፣ አዲስ አበባ ለመግባት በሩ ክፍት መሆኑን ባስታወቁ 24 ሰዓት ሳይሞላ፣ ከአዲሱ የድርድር ሃሳብ ጋር በተያያዘ ይሁን በሌላ ጌታቸው ረዳ ዛሬ ” … have been consistent in our principled position on the need for dialogue to end the crisis peacefully. ትህነግ ቀውሱን በሰላማዊ መንገድ በንግግር ለመፍታት አቋማችንና መርሃችን እንደተጠበቀ ነው” ሲል በቲውተር ገጹ ላይ አስፍሯል። በዚህ የቲውተር መልዕክቱ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ለንግግር ዝግጁ እንዳልሆኑም አመልክቷል።
ኢትዮጵያ ውስጥ ሕዝብ በራሱ አነሳሽነት ለቁጥር በሚገርም ደረጃ ወደ ወታደር ማሰለጠኛ ጣቢያዎች መትመሙ፣ የደጀኑ ድጋፍና ወላጆች ልጆቻቸውን መርቀው መላካቸው በሚዲያ ይፋ ከሆነ በሁዋላ፣ አቶ ጌታቸው የሰላምና የንግግር ሃሳብና መርህን ደጋግመው መናገራቸው፣ ከዚሁ ጎን ለጎን ከተቱን የትግራይ ሕዝብን ለማጥፋት የሚደረግ ዝግጅት አድርገው መሳላቸው የዛሬ ጠዋት መነጋገሪያ ሆኗል።
መንግስት በተደጋጋሚ እንዳስታወቀውና የክልል መንግስታት በይፋ እንደተናገሩት ” ጉዳያችን ትህነግ ከሚባል አሸባሪ ጋር ነው” በማለት እየገለጹ ባለበት ሁኔታ ጌታቸው ጉዳዩን የትግራይን ሕዝብ ከማጥፋት ጋር ማገናኘቱ ” እንደተለመደው የትግራይን ህዝብ ፍርሃት ውስጥ በመጣል በሁለት አማራጭ ውስጥ ሆኖ ውጊያ እንዲመርጥ ለማድረግ ነው” የሚል አስተያየት ተሰጥቶበታል።
አዲስ አበባ የገቡት የአሜሪካ መልዕተኞች ምን ላይ እንደደረሱ በይፋ ተባባሪያችን ባያረጋግጥም፣ ወልቃይትን ጨምሮ የድንበርና የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ቦታዎች መፍትሄ እስኪገኝ በፌደራል ስር እንዲሆኑ፣ የፌደራል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ወደ ትግራይ እንዲገቡ፣ የመብራት፣ የባንክ፣ የስልክ ወዘተ አገልግሎቶች እንዲጀመሩ፣ የትግራይ መልሶ ማቋቋም ልዩ ፕሮግራም እንዲነደፍ… የመሳሰሉት ጉዳዮች ተነስተዋል።
በመንግስት በኩል የተሰጠውን ዝርዝር ምላሽ መረዳት ባይቻልም፤ የተጀመረው ኢትዮጵያን በመከላከያ ሃይል ማግዘፍና ካለችበት ከበባ ባስቸኳይ እንድትወጣ የተጀመረው ንቅናቄ ለአፍታም እንደማይቆም፣ ዝግጅቱ የኢትዮጵያን ሕዝብ ከማንኛውም ስጋት በጥቂት ወራቶች ነጻ ማድረግ፣ በአገሪቱ ውስጥ የሚነቀሳቀሱ ማናቸውንም ታጣቂዎች ለመጨረሻ ጊዜ ለማስወገድ ያለመ ስለመሆኑ ዘጋቢያችን መረጃ አግኝቷል።
መንግስት በይፋ ለሰላማዊ ንግግር ክፍት መሆኑ፣ ህግ የሚገልጋቸው በህግ እንደሚጠየቁ ደጋግሞ ከመናገሩ ውጭ አሁን ትህነግ ጠየቀ ስለተባለው የሰላም ነግግር በይፋ ያለው ነገር የለም።
የሰሞኑ የሕዝብ ንቅናቄና ወዶ ዘማችነት በመላው አገሪቱ እንደ ማዕበል መነሳቱ አሜሪካንን ጨምሮ በርካታ አገሮችን ማስደንገጡ እየተዘገበ ነው። የሽግግር መንግስት በሚል እነ አቶ ልደቱና ሻለቃ ዳዊት ባዘጋጁት ዕቅድ ውስጥ ስማቸው የሚነሳ ሳይቀር ራሳቸውን እያገለሉ መሆኑ ምን አልባትም ከህዝቡ ቁጣ የተነሳ ሊሆን እንደሚችል ግምት አለ።
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች በስሟ የሚገዘቱት እንጀራዋን ለመብላት እንጂ መከራዋን ለመካፈል… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤ ወንጌላዊ መኾን መልካም ነው፣ ወንጀለኛ መኾን ግን ሐጥያት… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣ እንዲሁም ትኩረቴ በቀላሉ ይከፋፈል ነበር። ሐኪሜ የብረት ማዕድን… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን ለጎን የትግራይ ከፍተኛ ባለስልጣናትና የዞን አስተዳዳሪዎች… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች ዜና የሚያቀብሉና እነሱኑ የሚከተሉ ስምምነቱ መክሸፉንና… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት