” የሰማ ዕረፍት” ሲሉ የትህነግ ሃይል የገደላቸውን ወገኖቻቸውን ምስል ይዘዋል። ህጻናት የተፈናቀሉ ስደተኞች ቢሆኑም የዓለሙ የስደተኞች ድርጅት አንዳችም ድጋፍ እንዳላደረገላቸው በጽሁፍ ያሳያሉ። ስደተኞች እንጂ ወንጀለኞች አለመሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት እንዲያይላቸው፣ እዲሰማ ደጁ ቆመዋል። የኤርትራ ተፈናቃይ ሰደተኞች።
አንድ ጠይው ሕጻን ማስክ አድርጋ ” እነዛ በትግራይ ካምፕ ያሉ ባስቸኳይ ወደ ሰላማዊ ስፋር ይዛወሩ” ስትል ትጠይቃለች። ከጎኗ ” እኛ ስደተኞች ነን። እኛም እንደ እናንተ ሰዎች ነን” ትላለች። በርካታ ልብ የሚነኩ መፈክሮች የያዙት የኤርትራ ስደተኞች በተባበሩት መንግስታት ቢሮ ደጅ ቆመው ” የህግ ያለ” ሲሉ ላየ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ቢለኔ ስዩም ” ዓለም ትህነግን ዝም አለው። ለለም፣ ለምን፣ ለምን…?” ሲሉ የጠየቁት ጥያቄ አግባብ መሆኑንን ይረዳል። ግን ለምን የኤርትራ ስደተኞች በዓለሙ የስደተኞች ካምፕ ስር ሆነው ሳለ ይገደላሉ? ይንገላታሉ? ይዘረፋሉ? ይፈናቀላሉ? በሚደርስባቸው ግፍ መጠንስ ስለምን ተቆርቋሪ አጡ? የቢለኔ ስዩም ብቻ ሳይሆን የሁሉም ጥያቄ ነው።
በአዲስ አበባ የሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኞች በትግራይ ክልል ኤርትራዊያን ስደተኞች ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍና እንግልት በመቃወም ሠላማዊ ሠልፍ ሲያካሂዱ ያነሱት ጥያቄ ይህንኑ ” ለምን ዝም እንባላለን?” የሚለውን ነው። ኤርትራዊያኑ ስደተኞች በአዲስ አበባ በሚገኘው የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ድርጅት መስሪያ ቤት ተገኝተው ላሰሙት ጩኸት የተሰጠው ምላሽ ምን እንደሆነ አልታወቀም።
በኤርትራዊያን ስደተኞች ላይ የሚደረግ ጥቃት ይቁም’፣ ‘ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ድምፃችንን ይስማ’፣ እና ሌሎችንም መፈክሮች በመያዝ የተቃውሞ ድምጻቸውን አሰምተዋል።
ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በትግራይ ክልል የሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኞችን ከሚደርስባቸው ግፍና በደል እንዲታደጋቸውም ጥሪ አቅርበዋል።ስደተኞቹ ከዚህ ቀደም በተለያየ ጊዜ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና ለመንግስታቱ የስደተኞች ድርጅት በደብዳቤና በአካል በመገኘት መልዕክት ብናስተላለፍም ምላሽ አላገኘንም ሲሉ ምሬታቸውን አሰምተዋል።
በትግራይ ክልል በሚገኙ ስደተኞች ላይ ግፍና እንግልቱ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱ፣ ስደተኞች እየተገደሉና በየጫካው በሽሽት ላይ ያሉትም ለከፋ ችግር እየተጋለጡ በመሆኑ አፋጣኝ መፍትሄ ይሰጠን ሲሉም ጠይቀዋል።
በሠላማዊ ሠልፉ ላይ አካል ጉዳተኞች፣ ሕፃናትና አዛውንት መሳተፋቸውን ኢዜአ ያተመው ምስል ያስረዳል። አሜሪካ በትናትናው ዕለት የኤርትራ ስደተኞች ጉዳይ እንደሚያሳስባት አምጣ፣ አምጣ ማስታወቋ አይዘነጋም።
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች በስሟ የሚገዘቱት እንጀራዋን ለመብላት እንጂ መከራዋን… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤ ወንጌላዊ መኾን መልካም ነው፣ ወንጀለኛ መኾን ግን… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣ እንዲሁም ትኩረቴ በቀላሉ ይከፋፈል ነበር። ሐኪሜ የብረት… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን ለጎን የትግራይ ከፍተኛ ባለስልጣናትና የዞን… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች ዜና የሚያቀብሉና እነሱኑ የሚከተሉ ስምምነቱ… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት