” የሰማ ዕረፍት” ሲሉ የትህነግ ሃይል የገደላቸውን ወገኖቻቸውን ምስል ይዘዋል። ህጻናት የተፈናቀሉ ስደተኞች ቢሆኑም የዓለሙ የስደተኞች ድርጅት አንዳችም ድጋፍ እንዳላደረገላቸው በጽሁፍ ያሳያሉ። ስደተኞች እንጂ ወንጀለኞች አለመሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት እንዲያይላቸው፣ እዲሰማ ደጁ ቆመዋል። የኤርትራ ተፈናቃይ ሰደተኞች።
አንድ ጠይው ሕጻን ማስክ አድርጋ ” እነዛ በትግራይ ካምፕ ያሉ ባስቸኳይ ወደ ሰላማዊ ስፋር ይዛወሩ” ስትል ትጠይቃለች። ከጎኗ ” እኛ ስደተኞች ነን። እኛም እንደ እናንተ ሰዎች ነን” ትላለች። በርካታ ልብ የሚነኩ መፈክሮች የያዙት የኤርትራ ስደተኞች በተባበሩት መንግስታት ቢሮ ደጅ ቆመው ” የህግ ያለ” ሲሉ ላየ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ቢለኔ ስዩም ” ዓለም ትህነግን ዝም አለው። ለለም፣ ለምን፣ ለምን…?” ሲሉ የጠየቁት ጥያቄ አግባብ መሆኑንን ይረዳል። ግን ለምን የኤርትራ ስደተኞች በዓለሙ የስደተኞች ካምፕ ስር ሆነው ሳለ ይገደላሉ? ይንገላታሉ? ይዘረፋሉ? ይፈናቀላሉ? በሚደርስባቸው ግፍ መጠንስ ስለምን ተቆርቋሪ አጡ? የቢለኔ ስዩም ብቻ ሳይሆን የሁሉም ጥያቄ ነው።
በአዲስ አበባ የሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኞች በትግራይ ክልል ኤርትራዊያን ስደተኞች ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍና እንግልት በመቃወም ሠላማዊ ሠልፍ ሲያካሂዱ ያነሱት ጥያቄ ይህንኑ ” ለምን ዝም እንባላለን?” የሚለውን ነው። ኤርትራዊያኑ ስደተኞች በአዲስ አበባ በሚገኘው የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ድርጅት መስሪያ ቤት ተገኝተው ላሰሙት ጩኸት የተሰጠው ምላሽ ምን እንደሆነ አልታወቀም።
በኤርትራዊያን ስደተኞች ላይ የሚደረግ ጥቃት ይቁም’፣ ‘ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ድምፃችንን ይስማ’፣ እና ሌሎችንም መፈክሮች በመያዝ የተቃውሞ ድምጻቸውን አሰምተዋል።
ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በትግራይ ክልል የሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኞችን ከሚደርስባቸው ግፍና በደል እንዲታደጋቸውም ጥሪ አቅርበዋል።ስደተኞቹ ከዚህ ቀደም በተለያየ ጊዜ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና ለመንግስታቱ የስደተኞች ድርጅት በደብዳቤና በአካል በመገኘት መልዕክት ብናስተላለፍም ምላሽ አላገኘንም ሲሉ ምሬታቸውን አሰምተዋል።
በትግራይ ክልል በሚገኙ ስደተኞች ላይ ግፍና እንግልቱ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱ፣ ስደተኞች እየተገደሉና በየጫካው በሽሽት ላይ ያሉትም ለከፋ ችግር እየተጋለጡ በመሆኑ አፋጣኝ መፍትሄ ይሰጠን ሲሉም ጠይቀዋል።
በሠላማዊ ሠልፉ ላይ አካል ጉዳተኞች፣ ሕፃናትና አዛውንት መሳተፋቸውን ኢዜአ ያተመው ምስል ያስረዳል። አሜሪካ በትናትናው ዕለት የኤርትራ ስደተኞች ጉዳይ እንደሚያሳስባት አምጣ፣ አምጣ ማስታወቋ አይዘነጋም።
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ። አሁን ምኑ ነው አፍሪካ ህብረትን ስጋት… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች
- የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋልየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ። የዕዳ ጫናውን ለማቃለል የባንክ ወልዱም ጭምር ተፅእኖ እያሳደረ መሆኑም ተመልክቷል። የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል… Read more: የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋል
- ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁመግቢያ ሽግግር ፍትህ ጉልህ የመብት ጥሰቶች በተፈፀመባቸው ሀገራት ተጠያቂነትን ለማስፈን እና ተበዳዮችን ለመካስ ጥቅም ላይ ሲውል ቆይቷል፡፡ በሀገራችንም የሽግግር ፍትህ አስፈላጊነት ታምኖበት ፖሊሲ ሲዘጋጅ… Read more: ዋና ዋና የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ይዘቶች – ሲጨመቁ
- “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”“የሚሊሻ ኀይሉን በተመለከተ የሚዘዋወረው መረጃ ፍጹም መሠረተ ቢስ ነው” ሲሉ ኮሎኔል ግርማ ገሰሰ አስታወቁ። “ቅጥፈት ነው” ያሉትና በፕሬዚዳንቱ ስምና ፊርማ የተሰራጨው ደብዳቤ የሚሊሻ ሃይሉ… Read more: “የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ትጥቅ ይፍቱ በሚል የሚሰራጩ መረጃዎች ‘ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው’ ከሚል ቅዠት የተወለደ ቅጥፈት ነው”
- “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን“የትግራይ ተወላጆች ትህነግ ለፈጸመው ወረራ፣ ዘረፋ፣ ማፈናቀልና የግድያ ተግባራት የተቀናጀ የፖለቲካና የሚዲያ ድጋፍ ሰጥተዋል። በተለይም በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ ሮማናት አደባባይ ላይ የተለመደው አይነት… Read more: “የህዝባችንን ድምጽ የሚቀማና የሚያፍን የ’አማራ ስብስብ’ ለአማራ ክልል ተግዳሮት ሆኗል… ትህነግ ዘርፎ እያጋጋዘ ነው” አብን