Site icon ETHIO12.COM

በጎንደር ጥብቅ ውሳኔ ተላለፈ

የጎንደር ከተማ የጸጥታ ምክር ቤት ጥብቅ መመሪያ ማስተላለፉን አስታወቀ። በመመሪያው እንደተጠቀሰው ጤናማ፣ በሥነ ምግባር የታነጸ ትውልድ ለመገንባት ሲባል በከተማዋ ከጫት ጋር በታያያዘ ደንግጓል። ድንጋጌውን የሚተላለፉ እንደሚቀጡ ይፋ ተደርጓል።

ሀገርን ከጥቃት እና ከወረራ እንዲሁም ከጥፋት መታደግ የሚቻለው ከሱስ የፀዳ በሥነ ምግባር የታነፀ በመሆኑ ይህንን ትውልድ ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት መነሻ በማድረግ የጎንደር ከተማ የጸጥታ ምክር ቤት በጫት አቅራቢዎች አጓጓዦች፣ አከፋፋዮች፣ ቸርቻሪዎች፣ አስቃሚዎችና ተጠቃሚዎች ላይ የክልከላ ውሳኔዎችን አስተላልፏል ።

አሸባሪው የትህነግ ቡድን እና የትግራይ ወራሪ ከሌሎች ፅንፈኛ ፀረ ኢትዮጵያ ኀይሎች ጋር በመሆን ኢትዮጵያን ለማፈራረስ የክልላችን ሕዝብ ህልውናን አደጋ ላይ በመጣል ሕዝባችንን በወረራቸው አካባቢዎች በሙሉ ሁሉንም አይነት ግፎች እየፈፀመ ይገኛል።

ይህ ኃይል ኢትዮጵያን እንደ ሀገር ለማፈራረስ ካለው ህልም ባሻገር ከአማራ ሕዝብ ላይ የማወራርደው ሒሳብ አለኝ በሚል የተሳሳተ አስተሳሰብ መነሻ በማድረግ ወረራ በፈፀመባቸው የክልሉ አካባቢዎች በሕዝቡ ላይ የበቀል በትሩን ማሳረፍ ጀምሯል።

ይህን በማገናዘብ ወረራውን ሊመክት የሚችል የአካባቢውን ሰላም እና ደኅንነት አስተማማኝ እንዲሆን የሚያደርግ መንፈሰ ጠንካራ ወጣት ኀይል በሥነ ልቦና የተገነባ ትውልድ ደግሞ ሀገርን ከጥቃት እና ከወረራ እንዲሁም ከጥፋት መታደግ የሚቻለው ከሱስ የፀዳ በሥነ ምግባር የታነፀ በመሆኑ ይህንን ትውልድ ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት መነሻ በማድረግ የጎንደር ከተማ የጸጥታ ምክር ቤት በጫት አቅራቢዎች አጓጓዦች፣ አከፋፋዮች፣ ቸርቻሪዎች፣ አስቃሚዎችና ተጠቃሚዎች ላይ የክልከላ ውሳኔዎችን አስተላልፏል ።

በመሆኑም ከነሐሴ 28/2013 ዓ.ም ጀምሮ በከተማዋ ጫት ከሌላ አካባቢ ማጓጓዝ፣ መቸርቸር፣ ማከፋፈል፣ ማስቃምና መቃም ተከልክሏል። በመሆኑም ከነገ ጀምሮ ምክር ቤቱ ክልከላ ባደረገባቸው ተግባራት ላይ ሲሳተፍ የሚገኝ ተሽከርካሪ ግለሰብም ሆነ ድርጅት በሐረግ የሚጠየቅ መሆኑን ምክር ቤቱ በአክብሮት ይገልጻል።

ይህንን የከተማዋ የጸጥታ ኀይል ተከታትሎ እንዲያስፈፀም ታዟል።በጫት ንግድ የተሰማራችሁ የከተማችን የኅብረተሰብ ክፍሎች ዘርፍ ቀይራችሁ በሌሎች የንግድ የአገልግሎት እና ማኑፋክቸሪንግ ዘርፎች ለመሰማራት ባቋቋምነው ግብረ ኀይል አማካኝነት አስፈላጊውን ጥረት እና እገዛ የሚደረግ መሆኑን እናሳስባለን።

የጎንደር ከተማ ኮምዩኒኬሽን

“አብይ ባህር ዳር እንዳይመጣ ለማስጠንቀቅ ቦንቦች አፈንድተናል” ፋኖ – አብይ በባህርዳር ድልድይ መረቁ
በአባይ ወንዝ ላይ የተገነባው የ380 ሜትር ርዝመትና 43 ሜትር ስፋት ያለው ግዙፍ ድልድይ ምረቃ ስነስርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይና ሌሎችም ታዳሚዎች እንዳይገኙ ፋኖ በተመረጡ አራት ስፍራዎች ላይ ቦንቦች …
ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበች
አሜሪካ ተቀምጠው የኢትዮጵያን ሰላም የሚያውኩ ተፈላጊዎችን ሀገሪቱ አሳልፋ በመስጠት ትብብር እንድታደርግ የፌደራል ፖሊስ መጠየቁ ተገለጸ። በጀርመን በተመሳሳይ ስራ መጀመሩ የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ "ተፈላጊዎች" ተላልፈው እንዲሰጧት ጠየቀች፤ …
ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷል
ፈቃድ ሳይኖራቸው በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት አማረ እና ቤተሰቦቹ በተባለ ህንፃ ላይ ቢሮ ተከራይተው ሃሰተኛና የፈጠራ ወሬ ሲያሰራጩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች መያዛቸው ተገለጸ። ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት በህዝብ ጥቆማ …
“ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረ
በሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አካላት የሚዳክሩበት በዚህ ጦርነት የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር / …
Exit mobile version