Site icon ETHIO12.COM

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታወጀ – ሰርጎ ገቦችን ሕዝብ እየጠቆመ ነው

ልክ በደሴና ኮምቦልቻ እንደሆነው አስቀድመው ሰላማዊ በመምስለና በዓላማ ወዳጆቻቸው በመሸሸግ ወደ ከተሞች ያመሩ የትህነግ የሰራዊት አባላት መኖራቸው እንደታወቀ ተገልጿል። የአገር ደህንነትና ፖሊስ እነዚህ አካላት ላይም ሆነ በተመሳሳይ ከእነዚህ አካላት ጋር በድጋፍ በሚሰሩ ላይ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወሰድ አመልክተዋል። ሕዝብም ዙሪያውን እየተከታተለ በመጠቆም ላይ ነው። ከዚሁ ጋር በተያያዘ አስቸኳይ አዋጅ ታውጇል።

የትህነግ ሃይል ወደ መቀለ ከመለሱ በፊት አስቀድሞ ሃይሉ በሲቪል መልክ ወደ ከተማ ገብቶ በየመኖሪያ ቤቱ መመሪያ ይጠብቅ እንደነበር ያስታወቁ እንዳሉት አሁንም በጥቂት ሃይል እዛና እዚህ ብጥብጥ ፈጥሮ አዲስ አበባና ተመሳሳይ ከተሞችን ለመቆጣጠር ሃይል ማሰማራቱ ታውቋል። በደሴና ኮምቦልቻ የሆነው በገሃድ ከተገለጸ ወዲህ ሕዝብ ቁጣው እያየለ በመሄዱ ወደ ሌላ ግጭት እንዳያመራ መንግስት አስቸኳይ አዋጅ ማወጁ ደግ መሆኑንን ያመለከቱ አሉ።

ከመላው አማራ ሰፊ ቁጥር ያለው ሃይል ወደ ግንባር በየአቅጣጫው መዝመቱ፣ ተጨማሪ ሃይልም ለመዝመት ትራንስፖርት እየተጠባበቀ መሆኑ፣ ትህነግ በገባባቸው ቦታዎች አማሮችን እየመረጠ መጭፍጨፉ ተዳምሮ ቀጣዩን ትግል ” የመኖርና ያለመኖር” እንዳደርገው በመራር ቋንቋ እየተገለጸ መሆኑ ቀጣዩን ጦርነት ከቀደሙት ጊዚያቶች ሁሉ የመረረ እንዳያደርገው የፈሩም አሉ። ” ከለኩ አያልፍም፣ ያለቀው አልቆ ነጻነት” በሚል ፍርሃት ሳይሆን እልህ የሚያንበለብላቸው ” አሁን ፉከራ የለም” ሲሉ እየተደመጡ ነው።

ከአጎዋ ከዛሬ ነገ አግዳለሁ ስትል የቆየችው አሜሪካ በኮምቦልቻ ክ120 በላይ ንጹህ ዜጎች መረሸናቸውን በወጉ ሳይቃወም መላው አማራና ክልሎች ” ኢትዮጵያ ወይም ሞት፣ ትህነግን ዳግም መሸከም አንችልም” በሚል አቋማቸውን በመግለጽ ” ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር” ማለታቸው ሲታወቅ አሜሪካ ” ከአጎዋ ታግዳችኋል” ማለቷ ድራማውን በግልጽ ያሳየ ሆኗል።

ፌልትስ አማን የሚባሉት የምስራቅ አፍሪቃ ፊት አውራሪ ትህነግ ወደ አዲስ አበባ የሚያደርገውን ጉዞ እንደሚቃወሙ፣ ተቀባይነትም እንደሌለው አውስተው በነካ አፋቸው ኢትዮጵያዊያን የመረጡትን መንግስት ” ስልጣን ልቀቅ” የሚል ዓይነት መግለጫ ሰጥተዋል። ስትጠቃ ዝምታ፣ ስታጠቃ ወይም ለማጥቃት ጥርሷን ስትስል ማነቆ የሚጠብቅባት ኢትዮጵያ ዛሬ ልጆቿ በማምረራቸው ምን ሊሆን እንደሚችል ከወዲሁ ለማሰብ ከባድ ሆኗል። በዚህ ሁሉ ችግር የተከበበው መንግስት ዛሬ አዋጅ አውጇል። ክተቱም ተጠናክሮ ቀጥሏል።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በመላ ሀገሪቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጇል።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መምሪያ ዕዝ ምን ማድረግ ይችላል ?

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መምሪያ ዕዝ የሃገርን ህልውና እና ሉዐላዊነት፣ እንዲሁም የሰላማዊ ዜጎችን ደህነንት ለመጠበቅ አስፈላጊ ነው ብሎ ሲያምን ፦

የተከለከሉ ተግባራት እና ግዴታዎች ፦


Exit mobile version