Site icon ETHIO12.COM

መላላክ በየደረጃው አምልኮ ነው – ተላላኪዎች ሁሉ ሰጋጆች ናቸው

መላላክ ሱስ ነው።ከዛ በላይ ግን “አምልኮ” ነው። “ሌጋሲ ይሁን” የሚባለውም አምልኮ ስለሆነ ነው። መላላክና አሽከርነት ወደ ካንሰርነት እንደተለወጠ የአንጎል ኪንታሮት አይድንም። በመላላክ ውስጥ ያለው ስጋን የሚያደልብ፣ ፊትን የሚያወዛ የመቾት መገለጫ ህሊና የሚባለውን ትልቁን የህሊና ሚዛን ስለሚገድለው፣ መዳን እንኳን ባይቻል ለማገገም እንኳ የሙከራ እድል የማፈላለግ ዝንባሌን ያሳጣል። ስለዚህ ተላላኪነት እንደ ቲታኖስ (መመረዝ) እያሳበጠ የሚደፋ መንፈሳዊ ሞት ነው። ሰው የመንፈስ ውጤት ነውና መንፈሱ እንዲህ አሳብጦ የሚወስደው መንፈስ መጣፉ እንደሚለው የአራጁና የነጣቂው መንፈስ ነው። “ወደ ሲኦልም ወርደን” የሚያሰኘው የደም ግብሩ፣ የደም ምሱ መንፈስ ነው።

እንግዲህ ይህ መንፈስ የሚጨፍርባቸው ሁሉ እንደየደረጃው ተላላኪዎችና የላኩዋቸውን የሚተማመኑ ናቸው። ከስር ከጥልቁ የሚታዘዙት፣ ከታች የተቀበሉትን ትዕዛዝ ለማስፈጸም አንዴ ሲጠሩ ” ሰባት ጊዜ ሰባሰባቴ አቤት” የሚሉት፣ እነዚህን ” አቤት” ባዮች የሚታዘዙ የበታች ቅጥረ ነብሰ ገዳዮች፣ በየደረጃቸው የዚህ የማይድነው የአሽከርነት ካንሰር የተለከፉ እንደሆኑ ጥርጥር የለውም። ልዩነቱ የታዛዥነቱ መጥንና ረቂቅነት ካልሆነ በስተቀር ደም ስር የሚንደባለሉ ሁሉ ከላይ የተገለጠው መንፈስ ልጆች ናቸው። አባታቸውም የሉሲፈር ሽንት ነው። ተደፍረዋላ!!

አብዮታዊ ዴሞክራሲ ቀዳሚው የሃይማኖቱ ልብ ነው፣ የህይወት መስዋዕትነት የሚከፈልበት ብቻ ሳይሆን ከሚጠይቀው በላይ እየተሰጠው የሚሰገድለት ምትሃት ነው፤ ደም የሚገበርለት፣ አጥንት የሚከሰከስለት፣ ህጻናት ለዕርድ የሚቀርቡለት፣ ሴቶች ተደፍረው ደማቸው የሚሰዋለት፣ ወንዶች ታርደው ለማስተሰርያ በመባነት የሚቀርብለት፣ ‘ሒሳብ እናወራርድባችኋለን’ ተብለው የተፈረጁ ስቃያቸው ዘላለማዊ እንዲሆን የሚሸረገድለት፣ ርኩሰት ቅድስና የሆለት፣ እናት ልጆቿ መርቃ ለዕርድ የምትልክለት፣ አባት ልጁን የተገኘውን ሁሉ አስገድዶ እንዲደፍር አደፋፍሮ ለመላክ ቃልኪዳን የገባለት፣ እንደነ መለስ ዜናዊ ዓይነት በግምገማ ሰበብ አናዛዥ የነፍስ አባት ያለው ፤ ይህ በማንም የሚመለክ ሃይማኖት ሳይሆን በትህነግ የተፈጠረ በእያንዳንዱ ትህነግ ህይወትና ልብ የታተመ ከደምና ከአጥንቱ የተዋሃደ፣ የነፍሱ ልብ ምት፣ ከተወለደ እስኪሞት የሚተነፍሰው፣ ይህንን ካልተነፈሰ ሕይወቱ የምትቀጭ የሚመስለው ሁለተናዊ እምነት ነው። ፍልፈሎቹ ተላላኪዎችም የዚህ እምነት አደግዳጊ፣ አገልጋይና የሚፈገለውን ዓይነት ግብር የሚገብሩ መንፈሳዊ ባሮች ናቸው። በጽሁፉ የተገለጹት ሁሉ ማለት ነው ።

ለማጣቀሻ የተወሰደ

የሉሲፈር ሽንቶች የሚባሉት ዲቃሎቹ በየትኛውም ደረጃ ያሉትን ነብሰ ገዳዮች፣ በየትኛውም ክፍለ ዓለም ያሉትን አውዳሚዎች፣ የየትኛውም ብሄር አባል የሆኑትን ተላላኪ አረመኔዎች ያለ ልዩነት የሚያጠቃልል ነው። ነገር ግን ደረጃቸውና አቅማቸው፣ ስልታቸውና የስልታቸው ማስፈጸሚያ ሃብታቸው፣ ከሁሉም በላይ የተፈጠሩበት የሉሲፈር ሽንት ጠረን መለያየት “ረቂቅ” ያደረጋቸው ለየት ይላሉ። የውሪው ሉሲፈር ልጆች የባለ ዙፋኑንን ሉሲፈር ልጆች ያመልካሉ። የደፉላቸዋል። ልክ ለመልካሙ አባት እንደሚደረገው አምልኮ፣ በየአመዱና ስርቻው የተፈለፈሉት የውሪው ሉሲፈር ጫጩቶች ለባለዙፋኑ ሉሲፈር ልጆች ይገዛሉ። ለዚህ ነው ስጀምር እንዳልኩት መላላክ ” አምልኮ” የሆነው።

ዋናዎቹ በተላላኪዎቻቸው አማካይነት ከሩቅና ከቅርብ ሆነው፣ አንዳንዴም መሃል ገብቶ በደም ለመታጠብ ምክንያት ለማግኘት አምላኪዎቻቸውን አስቀድመው ያደራጃሉ። በዚህ መልክ ከሁሉም አቅጣጫ ሆነው በማይሞላው ውንጫቸው የንጹሃንን ደም ይጋታሉ። በሊቢያ፣ በኢራቅ፣ በየመን፣ በሲሪያ፣ አፍጋኒስታን … ዛሬ ደግሞ ዳግም ኢትዮጵያ ላይ!!

ራሱን የእነዚህ ወገኖች ታማኝ ተላላኪ አድርጎ የተፈጠረው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር፣ ተላላኪነቱ አምልኮ ሆኖበት ያፈራቸው ሁሉ ልክ በእሱ ቃል ኪዳን መሰረት እነዚህኑ ባለዙፋኖች አምላኪና ለነሱ ተንደባላይ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል። ይህ የሚያሳየው አምልኮው መሰረቱ የጸና፣ ማጣበቂያ ኬሚካሉ የፈረጠመ፣ እድሜው ረዥም ” በደምና በምንዛሬ” የተጋመደ መሆኑንን ነው።

ትህነግ ከ” አምላኮቹ” በየደረጃውና በየጊዜው የሚሰጠውን ” የጥልቁን ሃዋሪያዊ ተልዕኮ” ማስፈጸም የሚቻለው፣ መርዙን ልሶ የሚያቃምሳቸው የተፋውን የሚልሱለት ደቀመዛምርት ያስፈጉታልና በየአቅጣጫው ከተሰፈረለት ላይ እየሰፈረ መልምሏል። የምልመላው ትምህርት የተቀዳው ከቅጥፈት አባት ዙፋን ስር በመሆኑ ምልምሎቹን ቅጥፈት ግቶ፣ ጥላቻን አስታጥቆ፣ ግብሩ የሆነውን ደም እንዲያጎርፉለት ስለትና ጥይት አስታቅፎ አሰማርቷል። የዚህ የሃሰት ስብከትና መደለያ ረብጣ የሰከሩ ተላላኪዎች በየአቅጣጫው ተበትነው ለባለዙፋኖቹ ቀለብ የተደርደሩትን ሰፋፊ ጋኖች ደም ይሰፍራሉ። በቀለ ወያሳን ያርዳል፣ ቶሎሳ ጋሩምሳን ይገላል ….

ተላላኪነት እንደየ ደረጃው አምልኮ በመሆኑ ሸኔ ትህነግን እያመለከ የራሱን ልጆች ደም ይሰፍራል። ተላላኪነት ልቡናን የሚደፍን ክፉ ነቀርሳ በመሆኑ ሸኔ የናቱን ልጅ ለወያኔ መንፈስና አምልኮ ሲል ሲገብር ኩራት እንደተሰማው ተደርጎ ይቀርባል። በኦሮሞ ሞት ትህነግ እየጨፈረ ወደ መሃል ከተማ መምጣቱን ሲያውጅ፣ ኦሮሞን ነጻ እንደሚያወጣ ሲናገር፣ ከከበሮው ድምድምታ ውስጥ የሚሰማው የኦሮሞ እናት፣ ህጻናትና ሚስቶች ለቅሶ፣ ዋይታና ሃዘን ነው። ዳሩ ምን ያደርጋል የሸኔ ትግሬ አምላኪነት እንዳያይ፣ እንዳያስብ፣ እንዳያዳምጥ ልቡናውንና ህሊናውን ዘግቶታል። የሚለቅመው ትራፊ የስሜት ሃዋሳት አልባ አድርጎታል። የተኮላሹ፣ የተገደሉ፣ የተገረፉ፣ የተሰደዱ፣ አካላቸው የጎደለ … የኦሮሞ ልጆች እንደ ምናም ተቆጥረው ዛሬ ዳግም ትህነግ ኦሮሞ አናት ላይ እንዲወጣ ሸኔ ጭራውን ይቆላል። ይህ ለኦሮሞ ሃፍረት የሆነ የተላላኪነት መንፍስ የተጠናወተው ቅጥር ነብሰ ገዳይ የኦሮሞ ልጆችን ገሎና አስሮ “ኦሮሞ አጋንንት” ብሎ ሲራገምና ሲሳደብ የነበረውን ጌታቸው ረዳን ኦሮሞ ላይ ሊቆልል ይመኛል። ቄሮ ቀሬ መስሚያ የለውምና አይሳካም። በአማራ ዘንድም ተመሳሳይ ነው።

ትህነግ አማራን እንደሚጠላው ቃል ነበር። ቃሉንም ለመተግበር ይሞከር ነበር። አሁን ግን ቃል ተፈጽሟል። የትግሬ ወራሪ ሃይል አማራ ክልልን አውድሟል። አጥፍቷል። ዘርፏል። ህሳናትና አዋቂ ሳይመርጥ ደፍሯል። በጅምላ ቤታቸው፣ ደጃቸው ዘንድ ደርሶ ጨርሷቸዋል። ከብቶቻቸውን፣ እንስሶቻቸውን፣ መኖሪያቸውን፣ መገለገያቸውን፣ ሌማታቸውን፣ ሊጣቸውን፣ ዱቄታቸውን፣ እንኩሮዋቸው ሳይቀር ገልብጦ … ክሊኒክ፣ ሆስፒታል፣ ትምህርት ቤቶች፣ አገልግሎት መስጫ ተቋማትን፣ የመንግስትና የግል ሳይል መገለገያ የሆኑትን አግዟል። ያልቻለውን ከጥቅም ውጪ አድርጎታል። የክፋቱ መጠን ድመትና ውሻ ገሏል። መድሃኒት ጥቅም ላይ እንዳይውል በታትኖታል።

ይህ እየሆነ አማራውን ህበረት ፈትሮ መታደግ ሲገባ መላላክ አምልኮ የሆነባቸው እንግዴዎች በየስርቻው እየዶለቱ አማራው ራሱን እንዳይከላከል ይወተውታሉ። ያስጠነቅቃሉ። በርከሰው መንፈስ የተላላኪነት ቅንዝር ልባቸው ስለተሰረረና ከታችም ከላይም ሽንቁሮች በመሆናቸው ያያሉ ግን አያስተውሉም። ይሰማሉ ግን አያደምጡም። ይነገራቸዋል ይመከራሉ ግን የክፉ አምልኳቸው አንጥሮ ይመልሰዋል።

እኒህ የተላላኪነት አምልኮ “ዳፍንታም” ያደረጋቸውና መሰሎቻቸው በዚህ እጅግ አሳሳቢ ጊዜ ላይ አማራውን ሙሉ በሙሉ ላወደመ ሃይል የአምልኮ ሽንጣቸውን እየቆሉለት ነው። ሕዝብ እንደ ነበልባል በደል ገፍቶት ይህን ሃይል ሊያንቅ በተነሳበት ቅጽበት ” የሽግግር መንግስት” እያሉ በየአደባባዩ እርቃናቸውን ያፈነድዳሉ። ከላይም ሆነ ከታች ክፍት ላደረጋቸው ክፉ የኢያሪኮ ጩኸት ይጮሁለታል። ውለታቸው ውርደት፣ ስድብ፣ መደፈርና መሸንቆር መሆኑ ግልጽ ቢሆንም የተሰሩበት አምልኮ ክብራቸውን ስላስጣላቸው መላው አማራ ክብሩን እንዲጥል ከታወረ መንፈስ ጋር አድመው እንደ ጋግኖ ሲጮሁ ውለው ያድራሉ።

እንደ እሥሥት ራሳቸውን እየቀያየሩ ዘመን ያማይተካቸውን እውቅ አባት ፕሮፌሰር አስራትን ያስነጠቁን ሽፍታ አምላኪዎች፣ ቆመው መሄድ የማይገባቸው ሆኖ ሳለ ዛሬም ቆመው ለዳግም ” ቢንጎ” እንደ ካርድ አማራውን እየላጡ ሊጫወቱበት መንፈራገጥ ከጀመሩ ስንብተዋል። እነሱ ብቻ ሳይሆኑ ከመርፌ ቀዳዳ በጠበበ አመለካከት መከረኛ ዩቲዩብ ላይ ተሰቅለው የነዚህኑ ስልቦች ድምጽ የሚያራቡ በቀቅኖችም ተፈጥረዋል። የባለ ዙሃኖቹን መንፈስ እንዳለ ተግተው ቡችላ የፈለፈሉት ወንበዴዎች ዳግም ኢትዮጵያ እምብርት ላይ ሰንኮፋቸውን እንደ መልህቅ እንዲተክሉ የሚጮሁት በቀቀኖች ድካማቸው ከንቱ መሆኑ፣ በስተመጨረሻ ነገሩ ሁሉ ሲገለበጥ ” ለጊዜው አገር” የሚል ደም ደም የሚል ስላቅ ጀምረዋል። ገና ብዙ መገለባበጥ እናያለን።

እነ ክርስቲያን ታደለ፣ የሱፍ ኢብራሂም ጋሻው … ጀግኖቻቸው እንዳልነበሩ ዛሬ ግንባር ገብተው ህዝባቸውን ለመታደግ ምሳሌ በሆኑበት ሰዓት፣ እነዚህ ሽንቁር ተላላኪዎች ንዴታቸውን እያሰሙባቸው ነው። “ከገዢው የአማራ ፓርቲ ጋር እንድ ናቸው” በማለት አብንን ሲያቆሽሹ እየተደመጠ ነው። በስንት ለቅሶና እርዳታ ህዝብ ከነ ቤተሰቡ የታደገው ለማኝ ዛሬ ” በሬ ያኮላሸውን” እንዲሉ የሃሳብ ዘማች ሆኖላቸዋል።ግን እንዴት በዛ ደረጃ ( ይታወቃል) ጉዳት ደረብኝ ብሎ ሚስቱን ሲያስጮህ የነበረ ሰው ቢያንስ እንዴት ዝም አይልም? እንዴትስ ሚስቱ አትመክረውም? እንዴትስ አትቆጣውም? መታዘዝ አምልኮ ነው። ተላላኪነት መንፈስ ነው። ከታላቁ ሳይሆን ከትልቁ ዙፋን ስር የሚቀዳ የሚባለው ለዚህ ነው። ሰው የሁለት ጌቶች ሊሆን አይችልማ።

ዛሬ ጭንቅ ሲሆን ” ሰተት ብለው እንደገቡ፣ ሰተት ብለው ይውጡ” በሚል ሙግት የተከፈተው ከምንም በመነጨ አይደለም። ከተነደለ ስብዕና፣ ከተሸነቆረ ልቡናና ከሚያመልኩት የተላላኪነት መንፈስ ባርነት መላቀቅ አለመቻላቸው ነው። ይህ ደም ግብሩ የሆነ ቡድን አማራ ክልል ላይ የፈጸመውን ወንጀል ( ገና ሙሉ በሙሉ አልታየም) ለተከታተለ እንዴት እንዲህ ህግና ፍትህ እንዲበየን አይጠይቅም። የህሊና መድረመስ ማለት ይህ ነው። በነራችን ላይ በትግራይም ንጹሃን ላይ ቀደም ሲል በድል የፈጸሙ ህግ ሊጠይቃቸው ይገባል። ያ ማለት ግን ዛሬ አማራ ክልል ላይ ለተፈጸመው ዘግናኝ ጭፍጨፋ ማካካሻና እርቅ ማውረጃ ሊሆን አይችልም። የተድፈሩት ህጻናት አይተናቸዋል። ቢያንስ ንብረቱ ቢቀር እነሱ ላኡ ጥፋት ለፈጸሙ ተመጣኝና አስተማሪ ቅጣት ባስቸኳይ ግድ ነው።

አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቅ

ሰብለ ወንጌል ሃይሌ

ዘግጅት ክፍሉ – ይህ ጽሁፍ የጸሃፊዋ አቋምና አስተሳሰብ ብቻ ነው። የዝግጅት ክፉ አይደለም። ዝግት ክፍሉ አቋሙን የሚገልጸው በርዕሰ አንቀጽ መሆኑንን ለማሳሰብ እንወዳለን። ምላሽ ቢላክ እናስተናግዳለን

Exit mobile version