ወደ አገር ቤት የሚመጡ አንድ ሚሊዮን ዳያስፖራዎች የኢንቨስትመንት አማራጮችን የሚያዩበት መድረክ እየተዘጋጀ መሆኑን የኢንቨስትመንት ኮሚሽነሯ ሌሊሴ ነሜ አስታወቁ።
ኮሚሽነሯ ባለፉት አራት ወራት ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስት ማድረጋቸውንም ገልጸዋል።
ኮሚሽነር ሌሊሴ እንዳሉት በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ጥሪ ወደ አገር ቤት የሚገቡ ዳያስፖራዎች የኢንቨስትመንት አማራጮችን የሚያዩባቸው መድረኮች እየተዘጋጁ ነው።
መድረኮቹ በኢትዮጵያ ቅድሚያ በሚሰጣቸው የኢንቨስትመንት መስኮች ያሉ አቅሞችን ማየት የሚያስችሉ እንደሆኑም ገልጸዋል።
ኮሚሽኑ ዳያስፖራው መዋዕለ ንዋዩን ለማውጣትና በአገሩ የኢንቨስትመንት አማራጮች ለመሳተፍ ሲመጣ የሚስተናገድበት ራሱን የቻለ ዴስክ መክፈቱንም ገልጸዋል።
የዳያስፖራ አባላቱ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን ይዘው በመምጣት በአገር በቀል ኢንቨስትመንቶች ውስጥ እገዛ ሊያደርጉ የሚችሉበት ዕድል መኖሩንም ጠቁመዋል።
በተጨማሪም ዳያስፖራው ያልተነኩ የአገሪቷን የኢንቨስትመንት አማራጮች፣ የውጭ ባለሃብቶችን ኢንቨስትመንቶችና ተያያዥ ስራዎች እንዲጎበኝ ይደረጋል ብለዋል።
ኮሚሽነር ሌሊሴ በተጨማሪም ወደ አገር ቤት ያልገቡ የዳያስፖራ አባላት በኢትዮጵያ ኢንቨስት የማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው በተለያዩ መንገዶች እያሳወቁ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
ለዚህ ስኬትም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከዳያስፖራ ኤጀንሲና ከክልሎች ኢንቨስትመንት ቢሮዎች ጋር እየተሰራ ነው ብለዋል።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የተለያዩ ችግሮች ቢገጥሟትም በበጀት ዓመቱ አራት ወራት ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ኢንቨስትመንት መጀመራቸውን ነው የገለጹት።
በአማራና በአፋር ክልሎች በነበረው ጦርነት ስራ አቁመው የነበሩ የኢንቨስትመንት መስኮችን በማስተባበር ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ መሆኑንም ኮሚሽነር ሌሊሴ አስታውቀዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
- “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረው
- ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!
- ምን ያክል ተዘጋጅተናል? ጥድፊያ አገር አልባ ለመሆን !! ህጻናቱ ምን አጠፉ?
- የደም ግፊት በመለካትና ክትትል በማድረግ የስትሮክ ተጋላጭነትን መቀነስ
- የስኳር ህመም አይነቶች እና ምልክቶች