” ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን መገንባት የምንችለዉ በትጥቅ ትግል ሳይሆን በበሰለና በሰለጠነ ዉይይት ብቻ ነዉ። “- አቶ ሌንጮ ለታ
በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት የሚዘጋጀዉ 18ኛዉ ዙር የጉሚ በለል የዉይይት መድረክ ” የብሔራዊ ዉይይቱ አንኳር ጉዳዮችና ሃገራዊ ፋይዳዉ” በሚል ርዕስ ተካሄዷል።
ለዉይይት መድረኩ የተዘጋጀዉን የመወያያ ጽሁፍ ያቀረቡት በኦሮሞ ፖለቲካ ዉስጥ ትልቅ ከበሬታ የሚሰጣቸዉ አንጋፋዉ ፖለቲከኛ አቶ ሌንጮ ለታ ሲሆኑ በሃገራዊ ወይይቱ አስፈላጊነትና በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዙሪያ አንኳር ነጥቦችን አንስተዋል።
ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን መገንባት የሚቻለዉ በትጥቅ ትግል ሳይሆን በበሰለና በሰለጠነ ወይይት ብቻ ነዉ ያሉት አወያዩ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመገንባት ከጦርነት ይልቅ ሰላማዊ ወይይት ተመራጭ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሃገራዊ ዉይይቱ ለኦሮሞ ህዝብ በጣም አስፈላጊ መሆኑን የገለጹት አወያዩ ሃገራዊ ዉይይቱ በርካታ ድምጾችና ፍላጎቶች የሚንጸባረቁበትና የሚሰሙበት ሊሆን ይገባል ብለዋል።
እኩልነት በሌለበት አንድነትን መፍጠር አይችልም ያሉት አወያዩ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለመፍጠር ሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች ራሳቸዉን የሚመለከቱባትን ኢትዮጵያን መገንባት ይገባል ብለዋል።
ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን በሂደት እንጂ በአንድ ጊዜ መገንባት አይቻልም ያሉት አቶ ሌንጮ ለታ እንከን የሌለበት ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን መፈለግ የተሳሳተ አስተሳሰብ ነዉ ብለዋል።
አንዳንድ የዉይይቱ ተሳታፊዎችም ያለፉት ስርዓቶች ሲከተሉት የነበረዉ ፖለቲካዊ አስተሳሰብና ትርክት በሕዝቦች መካከል ልዩነት እንዲሰፋና አለመግባባት እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል ብለዋል።
ያለፉት ስርዓቶች በህዝቡ መካከል ጥለዉ ያለፉትን የተዛቡና ተቀባይነት የሌላቸዉ ትርክቶችንና አስተሳሰቦችን በማረም ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለመገንባት ሃገራዊ ዉይይቱ ትልቅ ድርሻ አለዉ ብለዋል።
ፖለቲከኞች: ጋዜጠኞች: አርቲስቶችና ምሁራን ለሃገራዊ ዉይይቱ ስኬት የድርሻቸዉን ሊወጡ እንደሚገባም ገልጸዋል።
ተሳታፊዎቹን ያወያዩት የኦሮሚያ ዳያስፖራ ዳይሬክተር አቶ አሚን ጁንዲ ሲሆኑ በዉይይት መድረኩ ላይ ታዋቂ የኦሮሞ ፖለቲከኞች: የሚዲያ አመራሮችና ጋዜጠኞች: አትሌቶች: አርቲስቶችና ሌሎች ተሳታፊዎች ተገኝተዋል። via OBN
ወንድማገኝ አሰፋ
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ