ተከሳሽ ዘማ ደባሽ የተባለችው በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የወንጀል ህግ አንቀጽ 447/ለ/ ላይ የተደነገገውን ድንጋጌ በመተላለፍ በፈፀመችው በሐሰት መወንጀል ዐቃቤ ህግ ክስ መስርቶባታል፡፡
የዐቃቤ ህግ የክስ መዝገብ እንደሚያስረዳው ተከሳሿ የሌላውን ሰው ንጽህና እያወቀች ጥቅምት 22 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት አካባቢ በአራዳ ክፍለ ከተማ ጋንዲ ሆስፒታል ምርመራ ክፍል በመስከረም ወር 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 አካባቢ ቴዎድሮስ አበበ የተባለ ግለሰብ ቤት ውስጥ በሰራተኝነት ተቀጥራ ስትኖር “አልጋ አንጥፊ ብሎ ጠርቶኝ አስገድዶ ደፍሮኛል” በማለት ቃል ሰጥታ ተጠርጣሪው ተይዞ ጊዜ ቀጠሮ ከተጠየቀበት በኋላ ታህሳስ 7 ቀን 2014 ዓ.ም ለኮልፌ ቀራኒዮ ፖሊስ መምሪያ ሴቶችና ህፃናት ምርመራ ክፍል ከቤቱ መውጣት ፈልጌ እንጂ አልደፈረኝም በማለት በድጋሜ ቃል የሰጠች በመሆኑ በፈፀመችው በሐሰት መወንጀል ወይም መክሰስ ወንጀል ተከሳለች፡፡
ዐቃቤ ህግ በበኩሉ ተከሳሿ የተከሰሰችበትን የወንጀል ድርጊት እንደ ክሱ ሙሉ በሙሉ ያመነች በመሆኑ ባመነችው መሰረት በተከሳሿ ላይ የጥፋተኝነት ፍርድ ይሰጥልኝ ሲል አቅርቧል፡፡ ፍርድ ቤቱም ተከሳሿ በተከሰሰችበት ድንጋጌ ስር በዝርዝር ያመነች በመሆኑ ባመነችው መሰረት ጥፋተኛ ነሽ ብሏታል፡፡
ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራኒዮ ምድብ ፈጣን የወንጀል ችሎትም ታህሳስ 13 ቀን 2014 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ በ1 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት እና አምስት መቶ ብር የገንዘብ መቀጮ እንድትቀጣ ሲል ወስኖባታል፡፡
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ።… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት