“አስገድዶ ደፍሮኛል” ስትል በሐሰት የወነጀለችው ተከሳሽ በፅኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጣች

ተከሳሽ ዘማ ደባሽ የተባለችው በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የወንጀል ህግ አንቀጽ 447/ለ/ ላይ የተደነገገውን ድንጋጌ በመተላለፍ በፈፀመችው በሐሰት መወንጀል ዐቃቤ ህግ ክስ መስርቶባታል፡፡
የዐቃቤ ህግ የክስ መዝገብ እንደሚያስረዳው ተከሳሿ የሌላውን ሰው ንጽህና እያወቀች ጥቅምት 22 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት አካባቢ በአራዳ ክፍለ ከተማ ጋንዲ ሆስፒታል ምርመራ ክፍል በመስከረም ወር 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 አካባቢ ቴዎድሮስ አበበ የተባለ ግለሰብ ቤት ውስጥ በሰራተኝነት ተቀጥራ ስትኖር “አልጋ አንጥፊ ብሎ ጠርቶኝ አስገድዶ ደፍሮኛል” በማለት ቃል ሰጥታ ተጠርጣሪው ተይዞ ጊዜ ቀጠሮ ከተጠየቀበት በኋላ ታህሳስ 7 ቀን 2014 ዓ.ም ለኮልፌ ቀራኒዮ ፖሊስ መምሪያ ሴቶችና ህፃናት ምርመራ ክፍል ከቤቱ መውጣት ፈልጌ እንጂ አልደፈረኝም በማለት በድጋሜ ቃል የሰጠች በመሆኑ በፈፀመችው በሐሰት መወንጀል ወይም መክሰስ ወንጀል ተከሳለች፡፡
ዐቃቤ ህግ በበኩሉ ተከሳሿ የተከሰሰችበትን የወንጀል ድርጊት እንደ ክሱ ሙሉ በሙሉ ያመነች በመሆኑ ባመነችው መሰረት በተከሳሿ ላይ የጥፋተኝነት ፍርድ ይሰጥልኝ ሲል አቅርቧል፡፡ ፍርድ ቤቱም ተከሳሿ በተከሰሰችበት ድንጋጌ ስር በዝርዝር ያመነች በመሆኑ ባመነችው መሰረት ጥፋተኛ ነሽ ብሏታል፡፡
ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራኒዮ ምድብ ፈጣን የወንጀል ችሎትም ታህሳስ 13 ቀን 2014 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ በ1 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት እና አምስት መቶ ብር የገንዘብ መቀጮ እንድትቀጣ ሲል ወስኖባታል፡፡
- «ድርድር አያዋጣንም ሀገሪቷን ማተራመስ አለብን» ታዋቂው ግብጻዊ ፓለቲከኛታዋቂው ግብጻዊ ፓለቲከኛ ኢትዮጵያን ስለማተራመስ – ኢትዮጵያ ውስጥ ኤምባሲ አያስፈልገንም – ፍትሃዊ የውሃ ድርድር የሚለው…
- ስምንት የነዳጅ ቦቴዎች ተወረሱየአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ሆን ብለው የነዳጅ እጥረት እንዲከሰትና ከመንግስት የተሰጠውን መመሪያና ደንብ ችላ…
- ሱዳን ትሪቡን ያሰራጨው አሳሳች ምስል!EthiopiaCheck Fact Check ሱዳን ትሪቡን የተባለ ድረ-ገጽ በትናንትናው ዕለት ‘Sudanese forces attack Ethiopian troops in…
- ከትግራይ የመጡ የሽብር ቡድኑ አባላት በቁጥጥር ሥር ዋሉከትግራይ ክልል የመጡ የሽብር ቡድኑ አባል የሆኑ ሁለት የልዩ ኃይል አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ። እነዚህ…
- ታዳጊ ሀገራት ከሩሲያ ማዳበሪያ እንዳይሸምቱ የአውሮፓ ህብረት ፕሮፖዛልአውሮፓ ህብረት ታዳጊ ሀገራት ከሩሲያ የሚያደርጉትን ግዢ በማገድ ግንኙነታቸውን ወደ ሌሎች ሀገራት ያደርጉ ዘንድ በህብረቱ…