የተባበሩት መንግስታት ከአስራ አምስት ጊዜ ላላነሰ ስብሰባ የተቀመጠለት የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር መቀመጫ የሆነውን መቀለን ረግጠው በተመለሱ ማግስት ባሌ ሲናና ወረዳ መታየታቸው ብስጭት መፍተሩ ተሰማ። ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ምሳሌ የሚሆን ልማት ላይ መሆኗን መመስከራቸው የስንዴን አብዮት ጉልበት ያሳየ ነው ተብሏል።
ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስር አብይ አህመድ በመሩት “ጉብኝት” የቀድሞው የናይጄሪያው ፕሬዝደንት ኦሊሴጎን ኦባሳንጆ በሲናና ወረዳ በ3 ሺህ 200 ሔክታር መሬት ላይ በክላስተር የለማውን የሥንዴ ማሳ መጎብነታቸው የተዘገበው በመንግስት መገናኛዎች ነው። የአፍሪካ ልማት ባንክና የዓለም ባንክ ሙሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ቃለ የገቡለትን የስንዴ እርሻ ኦባሳንጆ ” ለአፍሪካ ምሳሌ የሚሆን” ሲሉ ምስክርነታቸውን አሰምተዋል።
የስንዴ ፖለቲካ አስቀድሞ የገባቸው አብይ አሕመድ በቅርቡ ለፓርላማ ” ስንዴ ኤክስፖርት ማድረግ እንጀምራለን” በሚል ሲናገሩ ማታ ማታ “የዛሬ” እያሉ የሚተቹ ሲሳለቁባቸው ነበር። ከተቅላይ ሚኒስትሩ እግር እገር ስር እየተከተሉ ስራቸውን ሊያቆሽሹ የሚሞክሩትን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማታ የሚጮሁ እንቁራሪቶች ብዙ እንደሚመስሉ፤ ግን ሲያጠምዷቸው ከሶስት እንደማይበልጡ የሚናገረውን ምሳሌ ጠቅሰውላቸው እንደነበር አይዘነጋም።
“ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነች የሚገኘው ስራ አበረታችና ለበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ መሆን የሚችል ተግባር ነው” ሲሉ ምስክረነታቸውን እዛው ማሳው ላይ ሆነው የሰጡትይ አደራዳሪ፣ “ይህን ማለታቸው ከድርድሩ ጋር ምን ያገናኘዋል” በሚል ቁጣቸውን የገለጹባቸው ድምጻቸውን ያሰሙት ወዲያው ነው።
ስለጀመሩት ድርድር ልክ ዶክተር ለገሰና አምባሳደር ዲና እንዳሉት የጦርነቱ ሁኔታ መሻሻሉን፣ ሰብአዊ እርዳታ በብዛት መግባቱን፣ በጥቅሉ መሻሻል መታየቱንና ይህን መሻሻል ወደ ሚጸና የተኩስ አቁም ስምምነት ለማሸጋገር እንደሚተጉ፣ ነገር ግን ጊዜ እንደሚወስድ ከመግለጽ ውጪ ሌላ የተለየ አስተያየት አልሰጡም። ባንክና ኤሌክትሪክ መስለ አገልግሎቶች እንዲጀመሩ ቀደም ሲል ጀምሮ ሲሰማ የነበረውን ከመሰረታዊ መግባባት በሁዋላ ሊተገበር የሚችል አሳብ በድጋሚ ገልጸዋል። ኦባሳንጆ ለቢቢሲ ይህን ብለው ሲያበቁ በስንዴ ማሳ ውስጥ የአገሪቱ የደህንነት ሹም ባሉበት መታየታቸው ” በአፍሪቃ ቀነድ ዙሪያ መክረናል” ላሉት ክፍሎች በሽታ እንደሆነ ተሰምቷል።
“የአፍሪካ ሀገራት ለግብርናው ዘርፍ ትኩረት ሰጥተው ከሰሩ የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባሻገር ምርታቸውን ለውጭ ገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያቸውን ሊያሻሽሉ እንደሚችሉም ይህ ምስክር ነው” ሲሉ ለአገር ውስጥ ሚዲያዎች ያስታወቁት ኦባሳንጆ፣ ይህ አስተያየታቸው ከተሾሙበት ሃላፊነት የስራ ድርሻ ጋር አንዳችም ግንኙነት እንደሌለው ጠቅሰው ነቀፌታ ሰንዝረዋል። ትህነግም ደስተኛ እንዳልሆነ ቢሰማም በኦፊሳል ኦባሳንጆ ማሳ ጎብኝተው ” በሶፍ ኦማር ዋሻ ውስጥ ከቀረጻና ሳተላይት እይታ ውጪ ሆነው መሜስጠራቸው ሴራ ነው” ሲል አልተሰማም።
በ42 ሺህ 901 ሔክታር መሬት ላይ ተንጣሉ እስክስታ የሚወርደውን የስንዴ ነዶ ሲጎበኙ ” የደህንነት አለቃው አቶ ተመስገን ምን ይሰራሉ? ስንዴና እሳቸውን ምን አገናኛቸው” ሲሉ የጠየቁ ነገሩ ሌላ እንደሆነ፣ ለዓለም እንዲተላለፍ የተፈለገው አሳብና ዜናም የተለየ እንደሆነ ይገምታሉ።
ኦባሳንጆ በተሾሙበት የስልጣን ማዕቀፍ መቀለ እንደሆኑ በተገለጸ ማግስት ከኢትዮጵያ ባለስልጣናትና የደህንነት ሹም ጋር ማሳ እየጎበኙ መነጋገራቸው በትህነግ ላይ እየላላ የሄደ ጉዳይ መኖሩን እንደሚያሳይም የገለጹ አልታጡም። በተቃራኒ ግን ትህነግ ገና ከጅምሩ ” አልጣሙኝም” ያላቸውን ሰው ያወግዛል የሚል ግምት የሰጡ አሉ። እነዚህ ክፍሎች የቀድሞውን የናይጀሪያ ፕሬዚዳንት “ቺምፓንዚ” ሲሉ የትህነግ ደጋፊዎች መሳደባቸውንም ያስታውሳሉ።
የአፍሪካና የዓለም ባንክ አይናቸውን እንዳጠገበው የመሰከሩለት የስንዴ እርሻ ይበልጥ ሜካናይዝድ እንዲሆን፣ በሌለኦችም አካባቢዎች እንዲሰፋ ድጋፍ እንደሚያደርጉ በገለጹበት ቅጽበት፣ ኦባሳንጆ ” በኢትዮጵያ ከጦርነቱ ዜና በተለየ በልማት ላይ የሚሰራዉ ስራ ጎልቶ የወጣ ነው” ማለታቸው የአብይን መንገድ ስልትና ስሌት ሲረግሙ ለነበሩ ራስ ምታት፣ ለአድናቂዎቻቸው ደግሞ ” ልክ ነኝ” የሚል ምላሽ የሚያሰጥ ሆኗል።
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች በስሟ የሚገዘቱት እንጀራዋን ለመብላት እንጂ… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- “የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እየፈጸሙ ነው” – ትምህርት ቤቶችን ካምፕ አድርገዋልበአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች መመስከራቸውን ቢቢሲ አስታወቀ። ይህ የተገለጸው ከአለማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ከሃምሳ… Read more: “የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እየፈጸሙ ነው” – ትምህርት ቤቶችን ካምፕ አድርገዋል
- በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነውለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ መያዙንna ለዚህም ተግባራዊነት ከሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊየን በላይ ችግኝ መዘጋጀቱን ተገለጸ። 1… Read more: በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነው
- ” በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ወገኖቻችን አሁንም ሳይመሽ ቶሎ ወደ ድርድሩ እንዲገቡ በትህትና እንጠይቃለን ” ፕ/ር መስፍን አርአያየኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በሌላ መንገድ እየታገሉ ይገኛሉ ያላቸው አካላት ወደ ምክክር መድረኩ እንዲገቡ ጥሪ አቀረበ። ኮሚሽኑ ከዚህ ቀደም ተደጋጋሚ ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል።… Read more: ” በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ወገኖቻችን አሁንም ሳይመሽ ቶሎ ወደ ድርድሩ እንዲገቡ በትህትና እንጠይቃለን ” ፕ/ር መስፍን አርአያ