በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ውስጥ በአገሪቱ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጠበቃ ነኝ በማለት በርካታ ክሶችን ተከራክሮ የረታው ግለሰብ በባለሥልጣናት በቁጥጥር ስር ዋለ።
ግለሰቡን በተመለከተ የሚወጡ ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱት “ጠበቃው” ከመታሰሩ በፊት ከከፍተኛው ፍርድ ቤት ጀምሮ አስከ ይግባኝ ሰሚ ችሎት ድረስ 26 ጉዳዮችን ይዞ በመከራከር ለመርታት ችሏል።
ግለሰቡ ሊያዝ የቻለው ለኬንያ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር ተገቢው ትምህርት እና ብቃት ሳይኖረው በማስመሰል በዘርፉ በመሰማራቱ ከተለያዩ ሰዎች ጥቆማ ከደረሰው በኋላ ነው።
የሕግ ባለሙያዎቹ ማኅበር በማኅበራዊ ሚዲያ ገጹ ላይ እንዳሰፈረው ግለሰቡ፣ ጠበቃ እንዳልሆነ እና በኬንያ ውስጥ በጠበቅና እንዲሠራ የሚያስችለው ፈቃድ የሌለው ነው።
“ግለሰቡ በኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጠበቃ እንደሆነ እና የማኅበሩ አባል መሆኑን በመግለጽ ሲያጭበረብር ነበር” ሲል ማኅበሩ ከሷል።
የሕግ ባለሥልጣናት ጨምረውም ግለሰቡ ተገቢው ትምህርት እና ፈቃድ ሳይኖረው ለምን ያህል ጊዜ በጥብቅና እንደሠራ ባይገለጹም በርካታ ጉዳዮችን ለማሸነፍ መብቃቱ ተነግሯል።
ብሪያን ምዌንዳ በሚል ስም የሚታወቀው ይህ ግለሰብ ከዚህ ቀደም በአገሪቱ ውስጥ አሳሳቢ ሆኖ የነበረው “ሙንጊኪ” የተባለው የወንጀል ቡድን መሪን በመወከል በቴሌቪዥን በተለላፈ የፍርድ ሂደት ላይ ተሳትፎ እንደነበር ይነገራል።
ግለሰቡ ሐሰተኛ መሆኑ ከተነገረ በኋላም በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ይኽው ቪዲዮ በስፋት እየተዘዋወረ ይገኛል።
የኬንያ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር ግለሰቡ ተመሳሳይ ስም ያለውን ሕጋዊ ጠበቃ ግለ ታሪክ ከማኅበሩ ድረ ገጽ ላይ በመውሰድ እርሱን መስሎ ሲያጭበረብር ቆይቷል ብሏል። BBC
- “አብይ ባህር ዳር እንዳይመጣ ለማስጠንቀቅ ቦንቦች አፈንድተናል” ፋኖ – አብይ በባህርዳር ድልድይ መረቁበአባይ ወንዝ ላይ የተገነባው የ380 ሜትር ርዝመትና 43 ሜትር ስፋት ያለው ግዙፍ ድልድይ ምረቃ ስነስርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይና ሌሎችም ታዳሚዎች እንዳይገኙ ፋኖ በተመረጡ አራት ስፍራዎች ላይ… Read more: “አብይ ባህር ዳር እንዳይመጣ ለማስጠንቀቅ ቦንቦች አፈንድተናል” ፋኖ – አብይ በባህርዳር ድልድይ መረቁ
- ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበችአሜሪካ ተቀምጠው የኢትዮጵያን ሰላም የሚያውኩ ተፈላጊዎችን ሀገሪቱ አሳልፋ በመስጠት ትብብር እንድታደርግ የፌደራል ፖሊስ መጠየቁ ተገለጸ። በጀርመን በተመሳሳይ ስራ መጀመሩ የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት… Read more: ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበች
- ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷልፈቃድ ሳይኖራቸው በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት አማረ እና ቤተሰቦቹ በተባለ ህንፃ ላይ ቢሮ ተከራይተው ሃሰተኛና የፈጠራ ወሬ ሲያሰራጩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች መያዛቸው ተገለጸ። ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት በህዝብ… Read more: ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷል
- “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረበሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አካላት የሚዳክሩበት በዚህ ጦርነት የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር… Read more: “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረ
- Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?Mercenaries from Ethiopia’s Tigray People’s Liberation Front are fighting alongside Sudanese army regulars against fighters of the Rapid Support Forces (RSF), the paramilitary group is claiming. The… Read more: Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?