የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ አንድ ሺህ አንድ መቶ ሀኪሞችን ለመቅጠር ባለፈዉ ዓመት ሰኔ ወር 2015 ዓ.ም ያወጣውን ማስታወቂያ ተከትሎ ተመዝጋቢ ስራ ፈላጊ ሃኪሞች ባለማግኘቱ በጀቱን ማዛወሩን አስታወቀ። ሃኪሞች ከተመረቁ በሁዋላ ስራ ማጣታቸው በተደጋጋሚ የሚገለጸውን ሮሮ እንደነበር ይታወሳል።
“ቢሮው ማስታወቂያ ቢያወጣም ተቀጣሪዎችን ባለማግኘቱ በጀቱን ወደ ሌላ ዘረፍ ማዛወሩን ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታዉቋል” ሲል ገጹ እንዳስታወቀው ክልሉ የሃኪሞች እጥረት እንዳለበት ሃላፊው አስታውቀዋል።
የቢሮዉ ምክትል ሃላፊ ዶ/ር ጉሻ በለኮ በሰኔ 2015 ላይ 1ሺህ 1መቶ ሀኪሞችን ለመቅጠር ማስታወቂያ የወጣ ቢሆንም ተቀጣሪዎችን ባለማግኘቱ ቢሮዉ በጀቱን ለሌላ ጉዳይ ማዋሉን ቢያስታውቁም አሁንም ከተገኘ ሃኪም መቅጠር እንደሚፈልጉ ገልጸዋል። ይሁን እንጂ በምን ምክንያት ገበያው ላይ ሃኪም ማግኘት እንዳልተቻለ አላብራሩም። “ለሁለት ወራት ያክል ማስታወቂያዉን ክፍት ባደርግም ገበያ ላይ ተቀጣሪዎችን አላገኘሁም” ከማለት ውጭ ዝርዝር አላቀረቡም።
በክልሉ በተያዘው አሰራር በየአንዳንዱ ጤና ተቋም ሀኪሞች መኖር አለባቸው። በዚሁ መሰረት በገጠር ጤና ተቋማት ሃኪሞችን መድቦ ለማሰራት ማስታወቂያ ቢወጣም ሀኪሞችን ማግኘት አልተቻለም። በዚህም ሳቢያ በምትኩ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችን፣ አዋላጆችን እና ነርሶችን ለመቅጠር መገደዳቸውን ሃላፊው ገልጸዋል፡፡
“ከዚህ በፊት ለመላዉ ኦሮሚያ አገልግሎት የሚሰጡ የጤና ባለሙያዎች ቁጥር 72ሺህ ነበር” ያሉት ሃላፊዉ አሁን ላይ ቁጥሩ ወደ 85ሺህ ከፍ ማለቱን ግልጸዋል፡፡
“በተቻለን አቅም ማስታወቂያ አዉጥተን ገበያ ላይ የነበሩትን ለመዉሰድ ሞክረናል። ነገር ግን አሁንም የሀኪሞች ዕጥረት አለብን” ያሉት ሃላፊው፣ “ማስታወቂያዉን አይተዉ የመጡትን እንቀጥራለን ፤ካልመጡ ግን ገበያዉ ላይ የሰዉ ሃይል እንደሌለ ነዉ የሚቆጠረዉ” ብለዋል። ይህ ንግግራቸው “ተመርቀው ስራ አላገኙም፣ አይ ይህቺ አገር” በሚል ሲወቅሱና ሲያማርሩ የነበሩ አካላትን መረጃ ጥያቄ ውስጥ የሚጥል ሆኗል።
ሃላፊዉ በተጨማሪም ባለፈዉ ዓመት ሃኪሞችን ለመቅጠር ባወጣነዉ ማስታወቂያ ሀኪሞችን ማግኘት ስላልቻልን ወደ 7 መቶ አከባቢ የሚሆኑ የተለያዩ ባለሙያዎችን ቀጥረናል ሲሉም ነግረዉናል፡፡
ከኦርሚያ ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ አካባቢ አስተዳእሮች እንደሚሰማው ሃኪሞች ገጠር ገብተው ማገልገል አይፈልጉም። ምንም የሰላም ችግር በሌለባቸው አካባቢዎች እንኳን ቢሆን ለተወሰነ ጊዜ ገጠር ገብተው ያስተማራቸውን ህዝብ የማግለገል ተነሳሽነት የላቸውም። እርግጥ አስፈጊ የመኖሪያ ሁኔታዎች መሟላት እንዳለባቸው ቢታመንም “ገጠር ግብቶ የመስራት ፍላጎት ማጣት በአገር ደረጃ መነጋገሪይ፣ በማህበራቸው ዘንዳም አጀንዳ ሊሆን ይገባል” የሚሉ አሉ።
- “አብይ ባህር ዳር እንዳይመጣ ለማስጠንቀቅ ቦንቦች አፈንድተናል” ፋኖ – አብይ በባህርዳር ድልድይ መረቁበአባይ ወንዝ ላይ የተገነባው የ380 ሜትር ርዝመትና 43 ሜትር ስፋት ያለው ግዙፍ ድልድይ ምረቃ ስነስርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይና ሌሎችም ታዳሚዎች… Read more: “አብይ ባህር ዳር እንዳይመጣ ለማስጠንቀቅ ቦንቦች አፈንድተናል” ፋኖ – አብይ በባህርዳር ድልድይ መረቁ
- ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበችአሜሪካ ተቀምጠው የኢትዮጵያን ሰላም የሚያውኩ ተፈላጊዎችን ሀገሪቱ አሳልፋ በመስጠት ትብብር እንድታደርግ የፌደራል ፖሊስ መጠየቁ ተገለጸ። በጀርመን በተመሳሳይ ስራ መጀመሩ የሚታወስ ነው።… Read more: ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበች
- ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷልፈቃድ ሳይኖራቸው በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት አማረ እና ቤተሰቦቹ በተባለ ህንፃ ላይ ቢሮ ተከራይተው ሃሰተኛና የፈጠራ ወሬ ሲያሰራጩ ነበሩ የተባሉ… Read more: ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷል
- “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረበሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አካላት የሚዳክሩበት በዚህ… Read more: “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረ
- Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?Mercenaries from Ethiopia’s Tigray People’s Liberation Front are fighting alongside Sudanese army regulars against fighters of the Rapid Support Forces (RSF),… Read more: Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?