“የህግ የበላይነት ለማስከበር እየተወሰደ ያለዉን እርምጃ መቋቋም የተሳናቸው በሺዎች የሚቆጠሩ የአሸባሪዉ ሸኔ አባላት ለመንግስት እጅ ሰጡ” ሲል የዘገቡት መገናኛዎች እንዳሉት ድርጅቱ ቁመናው ፈርሷል።
በቅርቡ በታንዛንያ ለስምምነት ብዙ ርቀት ከተኬደና ከንግገሩ መልካም ዜና የተጠበቀ ባለበት ወቅት ስምምነት ላይ እንዳልተደረሰ መንግስት ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በሰላም ንግግሩ የተኩስ ማቆም ስምምነት ተደርሶ እንደነበር፣ አነጋጋሪ የነበረው የስምምነቱ ቴክኒካል አፈጻጸም ጉዳይና ታጣቂዎችን አስመልክቶ እንዴት ይስተናገድ የሚል እንደነበር ውይይቱን የሚከታተሉ አስታውቀው መግለጻችን ይታወሳል።
በሁሉም ረገድ እጅግ ተስፋ ሰጪ ስምምነት ላይ እየተደረሰ ቆይቶ በመጨርሻው ቀን ሙሉ የአቋም ለውጥ በማድረግ ከአመክንዮ ውጭ የሆነ ጥያቄዎችን በማቅረቡ ውይይቱ መጨናገፉ ይፋ ቢሆንም፣ ቀጣይ ንግግር እንደሚኖር ተጠቁሞም ነበር።
በታንዛንያ ንግግሩ እየተደረግ ባለበት ወቅትም ቢሆን ወታደራዊ ኦፕሬሽኑን ያላቋረጠው መንግስት በተለያዩ ቀናት ኦነግ ሸኔ ከፍተኛ ጉዳት እያስተናገደና ታጣቂዎቹ በተለያየ መጠን እጅ መስጠታቸው ሲገለጽ ስንብቷል። ብዙ ባይባልም መሳሪያ መማረኩንም በምስል የሚያሳዩ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር።
ዛሬ ኦቢኤን እንዳለው ከሆነ በሺህ የሚቆጠሩ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች እጅ ሰጥተዋል። እጃቸውን የሰጡት መከላከያ የሚያሳርፈውን ድብደባ መቋቋምና መመከት ባለማቻላቸው ነው።
“የተወሰደባቸዉን እርምጃ መቋቋም ተስኗቸዉ የተማረኩት ታጣቂዎች እንደ ተናገሩት ሸኔ ክፉኛ ተመትቶ በመፍረስ ላይ ይገኛል:” ያለው ሚዲያው “የሸኔ ኃይል በዉስጡ በተፈጠረዉ መከፋፈል እርስ በራሱ ወደ መጠፋፋት የተሻገረ በመሆኑ ለመንግስት እጅ ሰጥተናል” ሲሉ ታጣቂዎቹ ተስፋ መቁረጣቸውን አስታውቋል።
“ሸኔ የፍትህና የህዝብ ጥቅም ጠላት በመሆኑ እየፈረሰ ነው” ሲሉ እነዚህ የተማረኩትና በሰላም እጃቸዉን ለመንግስት የሰጡ የሸኔ ታጣቂዎች መናገራቸውን ዘገባው አክሎ ገልጿል። ይህን አስመልክቶ ኦነግ ሸኔ ይህ እስከታተመ ድረስ ማስተባበያ አልሰጠም።
- “አብይ ባህር ዳር እንዳይመጣ ለማስጠንቀቅ ቦንቦች አፈንድተናል” ፋኖ – አብይ በባህርዳር ድልድይ መረቁበአባይ ወንዝ ላይ የተገነባው የ380 ሜትር ርዝመትና 43 ሜትር ስፋት ያለው ግዙፍ ድልድይ ምረቃ ስነስርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይና ሌሎችም ታዳሚዎች እንዳይገኙ ፋኖ… Read more: “አብይ ባህር ዳር እንዳይመጣ ለማስጠንቀቅ ቦንቦች አፈንድተናል” ፋኖ – አብይ በባህርዳር ድልድይ መረቁ
- ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበችአሜሪካ ተቀምጠው የኢትዮጵያን ሰላም የሚያውኩ ተፈላጊዎችን ሀገሪቱ አሳልፋ በመስጠት ትብብር እንድታደርግ የፌደራል ፖሊስ መጠየቁ ተገለጸ። በጀርመን በተመሳሳይ ስራ መጀመሩ የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያ በአሜሪካ… Read more: ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበች
- ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷልፈቃድ ሳይኖራቸው በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት አማረ እና ቤተሰቦቹ በተባለ ህንፃ ላይ ቢሮ ተከራይተው ሃሰተኛና የፈጠራ ወሬ ሲያሰራጩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች መያዛቸው… Read more: ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷል
- “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረበሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አካላት የሚዳክሩበት በዚህ ጦርነት የትግራይ… Read more: “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረ
- Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?Mercenaries from Ethiopia’s Tigray People’s Liberation Front are fighting alongside Sudanese army regulars against fighters of the Rapid Support Forces (RSF), the paramilitary… Read more: Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?