ስያሜው ላይ ከፍተኛ ጥያቄ የሚነሳበት ሸኔ የተሰኘው ታጣቂ ቡድን አቅሙ መዳከሙና በድርጅት ደረጃ እየተፈረካከሰ መሆኑንን የሚያሳዩ መረጃዎች መውጣት ከጀመሩ በሁዋላ በተከታታይ ቀናት በርካታ ታጣቂዎቹ እጅ እየሰጡ ነው። በዛሬው ዕለት ብቻ በሆሮ ጉድሩ 110፣ በምዕራብ ሸዋ ዞን 120 እጅቸውን ሰጥተዋል። ከፍተኛ አመራሮች ሳይቀሩ በቀጣይ እጃቸውን እንደሚሰጡ አካሄዱን የሚከታተሉ እያስታወቁ ነው።
ሎንግ በሚለው ቅፅል ስሙ የሚታወቀው በምስራቅ ጉጂ ዞን የሸኔ የሎጂስቲክስና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ገመዳ ዱጎ ለመከላከያ ሠራዊት እጁን መስጠቱ በመንግስት መገናኛዎች በምስልና በቃለ ምልልስ ታጅቦ ሲቀርብ “ዜናው ከዜናም በላይ ነው” በሚል በቀጣይ የሚሰሙ መረጃዎች እንደሚኖሩ በፌብሩዋሪ 18፣ 2024 ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ የአውስትራሊያ ነዋሪ ጠቅሰን መዘገባችን ይታወሳል።
የቀድሞ የኦነግ መካከለኛ አመራር ” በዜናው ባልደሰትም። ትልቅ ኪሳራ ስለመሆኑ ጥርጥር የለውም። ውጤቱን በቅርቡ እናየዋለን” ሲሉ በወቅቱ መደመጣቸውም የሚዘነጋ አይደለም። መሳሪያ፣ ገንዘብ፣ ቀለብ፣ ልብስ፣ ህክምና፣ መድሃኒት ወዘተ ታዋጊዎቹ ባሉበት ሁሉ የሚደርስበትን አግባብ የሚመራና የሚያደራጅ አለቃና የሎጂስቲክ ሃላፊ መንግስት እጅ መግባት እንደተለመደው አይነት እንዳልሆነ ጠቁመው ነበር።
ሎንግ እጃቸውን ከሰጡና ” በቃኝ” በሚል ቃላቸውን ሲሰጡ ባልደረቦቻቸው የሳቸውን ፈለግ እንዲከተሉ ጥያቄና ትሪ አቅርበው ነበር። በይፋ ምክንያቱ ባይገለጽም በጉጂና አካባቢው የሸኔ ሃይሎች ዕለት ዕለት ክፉኛ ጉዳት እያስተናገዱና ይዞታቸውን እያጡ፣ ጥቂት የማይባሉ እጃቸውን ሲሰጡ እንደነበር የመከላከያ ማህበራዊ ገጽ በምስል እያስደገፈ ሲያስታውቅ ቆይቷል።
በመላው ኦሮሚያ በስፋት ተጀምሯል የተባለው ሸኔን የማሳደድ ዘመቻ ይፋ ከሆነ ጀመሮ በየዕለቱ በርካታ የምርኮ፣ የመደምሰስና በሰላም እጅ የመስተት ዜና ተስምቷል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የተዘጉ ፕሮጀክቶች መጀመራቸውን፣ የአየር መንገድ በረራ መጀመሩን፣ የተዘጉ መንገዶች በጊምቢና ደምቢዶሎ እንዲሁም በወላጋ የተለያዩ ዞኖች መከፈታቸውን የመንግስት ሚዲያዎች ሲያሳዩ ክርመዋል።
ይህ በንዲህ እንዳለ በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን በተለየዩ ወረዳዎች ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 110፣ በመዕራብ ሸዋ 120 የሚልቁ የአሸባሪው ሸኔ አባላት በተከታታይ ቀናት መንግስት ያቀረበውን የሳላም ጥሪ ተቀብለው እጃቸውን መስጥታቸው ይፋ ሆኗል። ከዚያም በየስፍራው እጅ የሚሰጡ ታጣቂዎች መበራከታቸው በማስረጃ እየተደገፈ እየወጣ ነው።
የሆሮ ጉድሩ ዞኑ አስተዳደር እንዳስታወቀው የመንግስት ጸጥታ ሃይሎች በተለያዩ ወረዳዎች በሚንቀሳቀሱ የሽብር ቡድኑ ሸኔ አባላት ላይ የተቀናጀ እርምጃ እየወሰዱ ሲሆን በተወሰደው የተጠናከረ እርምጃም 2 ሺህ 237 የሸኔ አባላት ሲደመሰሱ፣ 89 የሚሆኑት ደግሞ መማረካቸው አስታውቀዋል። ይህን አሃዝም ሆነ በተደጋጋሚ የሚሰማውን ዜና ድርጅቱ በየትኛውም መድረክ ሲያስተባብል አልተሰማም።
ወትሮ ታይቶ የማያውቅ ከባድ መሳሪያና የቡድን ተተኳሽ መማረኩ በምስል ተደጎ ከወጣ በሁዋላ ጃል መሮ በቅርቡ ማብራሪያ ሲሰጥ የተሰማበት መረጃ ሚዛን አንስቷል።
“ነገሮች ተበላሽተዋል” ሲል የተደመጠው ጃልመሮ ማብራሪያውን ለነማን እንደሚያቀርብ ባይታወቅም “ያረጁ” በሚል የሚወቅሳቸው ክፍሎች እንዳሉ ተሰምቷል። ጃልመሮ ከበድ ያለ ዜና ሲሰማ ቀደም ሲል በቢቢሲና አሜሪካ ሬድዮ ሲያደርግ እንደነበረው አላደረገም። ይልቁኑም ” የሚታዘዝ የለም። የሚሰማ የለም” ሲል ሰራዊቱ መፈረከሱን የሚያስረግጥ መረጃ ነው የሰጠው።
ጃልመሮ ከመንግስት ጋር በነበረው ድርድር ተሳትፎ ሲመለስ ተቃውሞ እንደገጠመውና አለምግባባቱ እንዳየለ የተሰማው ወዲያው ነበር። በአገር ቤት ያሉት የኦነግ ሰራዊት አብዛኛው አመራር በመርህ ደረጃ የሰላም ስምምነቱ እንደሚሳካ አስቀድሞ እምነት ነበራቸው። በጉዳዩ ላይ መረጃ እንደሚሉት ቅድመ ስምምነትም ነበር። በመጨረሻ ሰዓት ከአገር ቤት ለጊዜው ስማቸው የማይጠቀስ ነባር አመራር ስልክ በመደውል ” የሽግግር መንግስት ካልሆነ አትቀበሉ” በሚል የሰጡት መመሪያ ሳቢያ ድርድሩ መክሸፉ በታጣቂዎቹ አመራሮች ዘንዳ ለተከሰተው ልዩነትና የእርስ በርስ ግጭት ዋና ምክንያት እንደሆነ እነዚሁ ወገኖች ይናገራሉ።
ጃልመሮ “እጅህን ስጥ” በሚል ጀግንነቱን እያጣቀሰ ሲዝትበት የነበረ አንድ ሌላ አመራር በይፋ ቁጣውን ሲያሰማ ይፋ የሆነው ይህንኑ ልዩነት ተከትሎ ነው። አሁን ላይ እጃቸውን የሚሰጡና በሰላም የሚገቡ የሸኔ ታጣቂዎች የበዙት በዚሁ በውስጥ በተነሳው መከፋፈልና መከላከያ በሙሉ አቅሙ እየወሰደ ያለውን እርምጃ መቋቋም ባለምቻሉ እንደሆነ እጃቸውን የሰጡ እየገለጹ ነው።
መንግስት ከኬንያ ጋር ባደረገው ስምምነት የተነሳ ኬንያ በሯን መዝጋቷም እየተሰማ ነው። በኬንያ በኩል ያለው ኮሪዶር መዘጋቱ ጥቃት ለመቋቋም ማፈግፈግያና መደራጃ ያሳጣው ሸኔ ሁሉም ተዳምሮ በተስፋ መቁረጥ ውስጥ እንደሚገኝ መረጃ እየወጣ ነው። ጃልመሮ ” ነገሮች ተባልሽተዋል” እንዳለው በቅርብ ቀን የሚታወቁ አመራሮች እጃቸውን እንደሚሰጡ ከወዲሁ እየተሰማ ነው።
በኦሮሚያ ህዝብ በመሰላቸቱ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ለመከላከያ ድጋፍ ማድረጉንም እንደ አንድ ሌላ አንኳር ምክንያት የሚያነሱ በሆሮ ጉድሩ ብቻ ሳይሆን በምዕራብ ሸዋ ዞን 120 የኦነግ ሸኔ አባላት መንግስት፤ አባ ገዳዎች፤ ሃደ ሲንቄዎችና የሃገር ሽመግሌዎች ያቀረቡትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ለመንግስት እጅ መስጠታቸዉ የዚህ ውጤት እንደሆነ ይገልሳሉ። የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ዲዳ ጉደታም ያመለከቱት ይህንኑ ነው።
የማእከላዊ ኮር ምክትል አዛዥ ኮለኔል ጋዲሳ ዲሮ 53 ክላሽ፤ 4 መትረየስ፤ 20 ሽጉጥ፤ 17 ኋላ ቀር መሳሪያዎች እና ከ2ሺህ ጥይቶች ጋር የተማረኩ መኖራቸውን አመልክተዋ ፣ “እጃቸዉን የሰጡ የሸኔ አባላትም የሽብር ቡድኑ የትግል አላማ የኦሮሞን ህዝብ ነጻ የሚያወጣ ሳይሆን ይበልጥ ህዝቡን የሚያሰቃይ መሆኑን በመረዳታችን እጅ ለመስጠት ችለናል ብለዋል” ሲሉ ዜናውን ያሰራጩ መገናኛዎች ጽፈዋል።