Site icon ETHIO12.COM

የሐረሪ የምርጫ ሂደት በተመለከተ ምርጫ ቦርድ የሰጠውን ውሳኔ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውድቅ አደረገ

የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ አባላትን የምርጫ ሂደት በተመለከተ ምርጫ ቦርድ የሰጠውን ውሳኔ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውድቅ አደረገ

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ አባላት ከክልሉ ውጪ ባሉ የብሔሩ ተወላጆች የሚመረጡበት ሂደትን በተመለከተ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያስተላለፈውን ውሳኔ ውድቅ አደረገ። ፍርድ ቤቱ ዛሬ ማክሰኞ በዋለው ችሎት የጉባኤ አባላቱ የምርጫ ሂደት የሽግግር መንግስት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልሉ ህገ መንግስት በሚያስቀምጡት መሰረት እንዲካሄድ ሲል ወስኗል።

ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን የሰጠው ሁለት ጭብጦችን ከመረመረ በኋላ ነው። ምርጫ ቦርድ ጉዳዩ “ህገ መንግስታዊ ትርጓሜ የሚያሻ ነው። በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለማየት ስልጣን የለውም” በሚል ያቀረበውን መቃወሚያ የተመለከተው ፍርድ ቤቱ፤ የመከራከሪያ ጭብጡን ውድቅ አድርጎታል። ቦርዱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከዚህ ቀደም በጉዳዩ ላይ የሰጠውን ውሳኔ እና የሐረሪ ህገ መንግስትን መርምሮ ያስተላለፈውን ውሳኔ፤ “ከሐረሪ ክልል ውጪ ያሉ ዜጎች ቢመርጡ የሚደርሰውን አሉታዊ ተፅዕኖ ያላስረዳ ነው” በሚል ሳይቀበለው ቀርቷል።

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ ቤቱ ዛሬ ውሳኔውን ያስተላለፈው የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ፤ በምርጫ ቦርድ ውሳኔ ላይ የይግባኝ አቤቱታ ማቅረቡን ተከትሎ ነው። አቤቱታው የቀረበው፤ “የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ አባላት ከክልሉ ውጪ ባሉ የብሄሩ ተወላጆች መመረጥ አይችሉም” የሚለውን የምርጫ ቦርድን ውሳኔ በመቃወም ነበር። via (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

Exit mobile version