የያሬድ ጥበቡ ነገር
ብአዴን የተሰኘው ድርጅት በድን ሆኖ የኖረው ከአፈጣጠሩ ጀምሮ እንደ እስስት ተለዋዋጭ ባህሪ ባላቸው እንደ ያሬድ ጥበቡ( Yared Tibebu) አይነት ሰዎች በመመራቱ ይመስለኛል። አቶ ያሬድ ህወሓትን ከማምለኩ ውጪ በምንም ጉዳይ ላይ ጠንካራ አቋም ኖሮት አያውቅም። ዛሬ ያንቆለጳጰሰውን ነገ ተነስቶ ያለበቂ ምክንያት ሲቃወመው ታያለህ። ዝም ብሎ በነዱት ነው የሚነዳው።
(እንደ እኔ እንደ እኔ በየጊዜው አቋማቸውን የሚቀያይሩ ግልብ ሰዎች ሲያጋጥሙን እንደ ወንዝ ሳይሆን “እንደ ያሬድ ነው የሚነዱት” ብንል ሁላችንም ሊያግባባን የሚችል አገላለፅ ይሆናል ብየ አስባለሁ
ይህ ግለሰብ ከህወሓት አሽከርነቱ ተላቆ አሜሪካ መኖር ከጀመረ በርካታ አመታት ያስቆጠረ ቢሆንም አሁንም ድረስ ሞቶ የተቀበረውን ድርጅት ከማምለክ አልተመለሰም። በአንድ ወቅት “በረከት ስምኦን እና አዲሱ ለገሰ እንደ እንጀራ ይርቡኛል፤ እንደ ውሃ ይጠሙኛል” ብሎ ጉድ እንዳላስባለን አሁን ደግሞ ” ፃድቃን ገብረ ተንሳይ የአዲሱ የትግራይ ሰራዊት መሪ ሆኖ መምጣቱ በትግራይ ተስፋ እንዳልቆርጥ ያደርገኛል” ሲል እያስደመመን ይገኛል። ከወረዱ አይቀር እንደዚህ ነው።
ያሬድ እና መሰሎቹ ከሚፈፅሙት ድርጊት የተረዳሁት አንድ ነገር የወያኔ አሽከር ሆኖ ያገለገለ ግለሰብ በአካል ነፃ ቢወጣም አዕምሮው መቼም ቢሆን ከባርነት መላቀቅ የማይችል መሆኑን ነው። ለዚህም ይመስለኛል በመጦሪያ እድሜያቸው በረሃ የገቡት የቀድሞ ጌቶቹ ተአምር ይሰራሉ ብሎ ያመነው። አሁን እኮ አቶ ያሬድ የቀረው “መለስ ይመለሳል፤ ፃድቃን ያፀድቃል” ማለት ብቻ ነው
- Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?Mercenaries from Ethiopia’s Tigray People’s Liberation Front are fighting alongside Sudanese army regulars against fighters of… Read more: Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?
- Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAFSudanese warring party Rapid Support Forces has officially accused the Tigray People’s Liberation Front Fighters of… Read more: Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAF
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው