የብሄራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ከ700 ሺህ በላይ ኩንታል የምግብ ድጋፍ ወደ ትግራይ ክልል መላኩን አስታወቀ። መንግስት ይህን እያደረገ ” ረህብን ለፖለቲካ መጠቀሚያ ያደርጋል መባሉ አሳዛኝ ነው”
ካለፈው ወር አንስቶ በትግራይ ክልል የሚደረገው ሰብዓዊ ድጋፍ 86 በመቶ የቆዳ ስፋት በአጋር አካላት ቀሪው 14 በመቶ ደግሞ በመንግስት እንደሚሸፈን መገለፁ ይታወሳል። ይህ እውነት እያለ ነው መንግስት እርዳታን ለፖለቲካ እንደሚጠቀም የሚገለጸው።
በዚህም መሰረት ምዕራብ ዞን፣ ደቡብ ዞን አምስት ወረዳዎች፥ በመንግስት የሚሸፈኑ ሲሆኑ ደቡብ ሶስት ወረዳዎች፣ ደቡብ ምስራቅ፣ ምስራቅ፣ ማዕከላዊ፣ ሰሜን ምዕራብ እና የመቐለ ከተማ ደግሞ በአጋር አካላት የሚሸፈኑ መሆናቸውን የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል።
የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴ ለኢዜአ እንዳሉት ኮሚሽኑ በግጭትም ሆነ በሌሎች የአደጋ ክስተቶች ተጎጂ ለሆኑ ዜጎች ምግብና ምግብ ነክ ያልሆኑ ድጋፎች ያደርጋል።
ኮሚሽኑ በአማራ፣ ትግራይና ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልሎች ጊዜያዊ የአስቸኳይ ጊዜ ምላሽ ማስተባበሪያ ማዕከል በማቋቋም እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም በትግራይ ለ 4 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች የሶስተኛ ዙር ድጋፍ እየቀረበ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ድጋፉ በመንግስትና በዓለም ምግብ ፕሮግራም እንዲሁም መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ጥምረት እየተሰጠ መሆኑንም ነው የተናገሩት።
ቀደም ሲል ድጋፉ 70 በመቶ በመንግስት ቀሪው 30 በመቶ በአጋር አካላት ይቀርብ እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ 86 በመቶ በአጋር አካላት 14 በመቶ ደግሞ በመንግስት እየተሰጠ መሆኑን አብራርተዋል።
እስካሁን ባለው ለትግራይ ክልል 772 ሺህ 954 ኩንታል እህልና 289 ሺህ 339 ምግብ ነክ ያልሆነ ድጋፍ መላኩንም ጠቁመዋል።
ኮሚሽኑ ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ኀብረተሰቡ ተገቢውን ድጋፍ እንዲያገኝ እያደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።
ኮሚሽኑ በአማራና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎችም መሰል ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፥ ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ 124 ሺህ 49 ኩንታል እህል እንዲሁም በአማራ ክልል አጣዬ የተፈናቃዮች 32 ሺህ 520 ኩንታል ምግብ ተልኳል ብለዋል።
በዚህ መረጃ መሰረት መንግስት አስራ አራት በመቶ የሚሆነውን የቆዳ ስፋት ብቻ ለይቶ እርዳታ እየሰጠ ባለበት ሁኔታ ረሃብን ለፖለቲካ ፍጆታ እንዳዋለው ተደርጎ የሚነገረውን ዜና ውድቅ እንደሚያደርገው ባለሙያዎች እርዳታ ከሚሰጡትና ሃሰት ሪፖርት ለሚያደርጉት ክፍሎች አስታውቀዋል።
86 መቶኛውን የትግራይን የቆዳ ስፋት እርዳታ የሚመሩት ወገኖች ስለምን እንዲህ ያለውን ቅጥፈት ይናገራሉ? ለሚለው ምላሹ ሌላ እንደሆነና ሕዝብን ዛሬ ላይ ተንቅቆ እንደሚረዳው ባለያዎቹ አመልክተዋል።
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው።… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት