በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆች በወዳጅነት አደባባይ በመገኘት የብልፅግና ፓርቲን ወክለው ለህዝብ ተወካዮች እና ለአዲስ አበባ ምክር ቤት ከሚወዳደሩ እጩ ተወዳዳሪዎች ጋር ትውውቅ ማድረጋቸው ተገለጸ።
በመርሐግብሩ የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር አብርሃም በላይ፣ የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሀፍታይ ገብረ እግዚአብሄርን እና በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጅ የብልፅግና ፓርቲ ደጋፊዎችና አባላት ተገኝተዋል ።
የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት ብልጽግና ሁሉንም ኢትዮጵያዊያን ከዳር እስከ ዳር በማቀፍ በጋራ ሀገር የሚያስቀጥል ፓርቲ ነው ብለዋል ።
የትግራይ ህዝብ ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር በመሆን ኢትዮጵያን በመገንባት እና ዛሬ ላይ በማድረስ ትልቅ ሚና እንደነበረው ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል ።ከለውጡ በፊት በተለያየ መንገድ በተፈጠሩ ክፍተቶች የትግራይ ህዝብ በብዙ መልኩ ተጎጂ ነበር ያሉት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ አሁንም የትግራይ ህዝብ ዳር ተመልካች እንዲሆን የሚሹ ሃይሎች አሉ፤ ያለንበት ምዕራፍ ግን እውነት ከሀሰት እየተለየ የሚወጣበት ወቅት ነው ብለዋል።ለሁሉም ነገር ሰላም ወሳኝ በመሆኑ ሰላምን የሚያደፈርስን ማንኛውም እንቅስቃሴ በጋራ መመከት እንደሚገባም ጠቁመዋል ሲል የአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ዘግቧል።
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣ እንዲሁም ትኩረቴ… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን ዋስትና አፀና።… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት ውስጥ የሚኖሩ… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ