የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት በ08/04/2014 ዓ/ም በአብላጫ ድምፅ ያሳለፈውን ውሳኔ (ዓለም አቀፍ የመርማሪ ቡድን በኢትዮጵያ እንዲሰማራ) ኢትዮጵያ እንደማትቀበለው ፤ እንደማታስፈፅም፤ የትኛውም አይነት ትብብር እንደማታደርግ ማሳወቋ ይታወሳል።
የተመርማሪ ሀገር ፍቃድ በሌለበት የመርማሪ ቡድኑ ዕጣ ምን ሊሆን ይችላል ? ኢትዮጵያ ተገዳ መርማሪዎችን የምታስገናግድበት አሰራር ወይም ዓለም አቀፍ ህግ አለ ?
በዚህ ጉዳይ ለቪኦኤ አስተያየታቸውን የሰጡት ዶክተር አደም ካሴ (በተለይ በአፍሪካ የህግ እና ፖለቲካ ጉዳዮች ተንታኝ) ተከታዩን ብለዋል ፦
” በዓለም አቀፍ ህግ ይሄን ኮሚሽን በሚመለከት አንድ ሀገር ውስጥ ሊገባ የሚችለው / በሀገሪቱ ገብቶ ሊመረምር የሚችለው በሀገሪቱ ፍቃድ ከተሰጠው ብቻ ነው።
ኢትዮጵያን ሊያስገድዳት የሚችል ስርዓት የለም። ምንም እንኳን የህግ ስርዓት ባይኖርም በፖለቲካ ደረጃ ጫና ሊያመጣ የሚችል ፤ ምን የምትደብቁት ነገር አለ ? እየተባለ ፖለቲካዊ ጫናዎችን ሊያመጣብን ይችላል።
በህግ በኩል የኢትዮጵያ መንግስት እስካልተስማማ ድረስ ወደ ሀገር የመግባት መብት የላቸውም።
ሌላው ጉዳይ በአጠቃላይ በዓለም ደረጃ ከውሳኔ ሰጪ አካላት በተጨማሪ እነዙህ ውሳኔ አካላትን እየተጠቀሙ አንዳንድ ሀገራት እነሱ የሚደግፉትን አቋም ለማራመድ ይጠቀሙበታል።
በተለይ አሜሪካ እና ምዕራባውያን ኢትዮጵያ ይሄን ቡድን የማታስገባ ከሆነ አንዳንድ ጫናዎች ለማስረግ ለምሳሌ ማዕቀቦችን ለመጫን እና ግፉቶችን ለማድረግ ሊጠቀሙበት ይችላሉ።
ኢትዮጵያ በህግ ደረጃ ወደ ኢትዮጵያ ውስጥ የማስገባት ግዴታ ባይኖርባትም በተመድም ከዛም አልፎ ውሳኔውን የሚደግፉ ሀገራት ምዕራባውያን ሀገራትም ያንን ተጠቅመው ጫና ሊያደርጉ ይችላሉ።
ነገር ግን ወደ ኢትዮጵያ አይገቡም ማለት ምርመራውን ማድረግ አይችሉም ማለት አይደለም። ምርመራውን ማካሄድ ይችላሉ፤ ይቀጥላሉ በስልክም በሌላም መንገድ አካሂደው አለ የሚሉትን መረጃ ለምክር ቤቱ ያቀርባሉ። “
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
- “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረውየሚነሳው ጉዳዩ ልብ ሰባሪ ነው፣ ያስቃል፣ ያዝናናል፣ ያስገርማል፣ ያሳዝናል፣ ይቀፋል፣ ያሳፍራል፣ ለማመን ያስቸግራል … አንባቢ ስም ይስጠው።… Read more: “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረው
- ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!በፖለቲካም ሆነ በአካባቢያዊ አጀንዳ ነፍጥ ያነገቡ እና ጦርነትን አማራጭ አድርገው የሚንቀሳቀሱ ኢ -መደበኛ አደረጃጀቶች ሁሉ የጦር መሳሪያ… Read more: ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!
- ምን ያክል ተዘጋጅተናል? ጥድፊያ አገር አልባ ለመሆን !! ህጻናቱ ምን አጠፉ?ያለፈውን ግማሽ ምዕተ ዓመት የኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ሥነ መንግሥት ታሪክ በጥሞና የተከታተለ ኢትዮጵያዊ የግዛት አንድነቷን እና የፖለቲካ… Read more: ምን ያክል ተዘጋጅተናል? ጥድፊያ አገር አልባ ለመሆን !! ህጻናቱ ምን አጠፉ?
- የደም ግፊት በመለካትና ክትትል በማድረግ የስትሮክ ተጋላጭነትን መቀነስአንድ ሰው የደም ግፊት መጠኑ ከፍተኛ ከሆነ እና በጊዜው ሕክምና ካላደረገ ለከፍተኛ የልብ በሽታና በደም ዝውውር ማነስ… Read more: የደም ግፊት በመለካትና ክትትል በማድረግ የስትሮክ ተጋላጭነትን መቀነስ