በሀምሌ ወር 2013 ዓ/ም “ከአገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን የቀረበ የድርድር መነሻ ሀሳብ” በሚል የትግሬ ወራሪ አላማን በሚያራምደው ርዕዮት ሚዲያ መውጣቱ ይታወሳል። ሰነዱ በአገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ስም የትግሬ ወራሪን አላማ ማስፈፀም የሰሩት ነው። በዋነኛነት የትግሬ ወራሪ በሁመራ በኩል የትግራይ ክልል የሚቆጣጠረው ኮሪደር ይከፈትለት የሚል ነው። ወልቃይትና ራያ በውጭ አገር ጦር ይተዳደር ይላል። ይህን ሀሳብ መጀመርያ ስዬ አብርሃ አሜሪካ ለሚገኙ ሎቢስቶች አንስቶት እንደነበር ይታወቃል። ቀጥሎ ያሬድ ጥበቡ መፅሔት ላይ ቃል በቃል ፃፈው። ቀጥሎ እነ ልደቱ አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ነን ብለው ስማቸውን ሳይጠቅሱ የቴዎድሮስ ፀጋዬው ርዕዮት ሚዲያ ላይ አስነበቡት። ትናንት ማታ ልደቱ አያሌው ስማቸውን ደብቀው ያወጡት ሰነድ የእነሱ እንደሆነ በኢትዮ 360 ወጥቶ አምኗል። ያኔ ርዕዮት ያንብበው እንጅ ለ360 ደርሶ እንደነበር እናውቅ ነበር። በትናንቱ ውይይታቸው ልደቱ “ለእናንተም ልከንላችሁ ነበር” ይለዋል ኤርሚያስን። ያውቁ ነበር፣ ኤርሚያስ የፕሮጀክቱ አካልም ነው።
ከአምስት ወር በፊት ያ ሰነድ ሲወጣ፣ በነጋታው ስለ ስዬወወ ቡድን “አዲሱ ኢህዴን መጣልህ” ብዬ ረዘም ያለ ፅሁፍ ፅፌ ዘ ሀበሻ ላይ ተነብቦ ነበር። እነ ልደቱና ኤርሚያስ ለገሰም እንዳሉበት አስረድቸ ነበር። መረጃዎቹ ስለነበሩኝ በድፍረት ስልፅ ውሸት የመሰላቸው ወገኖችና የትግሬ ወራሪን አላማ ለማሳካት ደፋ ቀና እያሉ፣ ስለ ኢትዮጵያ እናስባለን የሚሉት ሴረኞች መንጋ ደግሞ ዘምቶብኝ ነበር። ዛሬ አቶ ልደቱን ማመስገን ይጠበቅብኛል። ራሱ ይፋ አድርጎታል። በወቅቱ ያን ሰነድ ለእነ ኤርሚያስም ልኮት እንደነበር ይናገራል።
እነ ልደቱ ያን ለትግሬ ወራሪ ወደ ሱዳን መውጫ በትግራይ ክልል የሚተዳደር ኮሪደር ይከፈትለት ያሉበት ሰነድ በድብቅ ካወጡ በኋላ ሀሳቡን ብዙ የሚገዛው ሲያጡ በይፋ መጥተዋል። ማንነታቸውን ከገለፁ በኋላ የመጀመርያውና ስማቸውን ያልገለፁበት ሀሳብ በተነበበበት ርዕዮት በአቶ ልደቱ አያሌው፣ ታሬድ ጥበቡና ታምራት ላይኔ ፎቶ ታጅቦ ተነበበ። ርዕዮት የትግሬ ወራሪን አላማ በቀጥታ ማራመድ ስለጀመረና እነ ያሬድና ታምራትም ስለተወቀሱ ተቀባይነት አጡ። በሶስተኛው የትግሬ ወራሪ ቡድንን አላማ ስልታዊ ሆኖ ወደሚያራምደው ኢትዮ 360 መጡ። ታምራትና ያሬድን ቆዩ ብለው ልደቱና ጎዳና የሚባል ሰው በኢትዮ 360 ቀረቡ። በቀደም ሁለቱ ቀርበው ስለ ድርድር አወሩ። አልበቃቸው ስላለ ትናንት ልደቱን ብቻውን አቀረቡት። ልደቱም የቀደመ ታሪካቸውን ሲያወሳ በአምስት ወር በፊት ስማችን ሳይጠቀስ ሰነድ አውጥተናል ብሎ አመነ። ድሮም የታወቀ ቢሆንም፣ ሰነዱ የእነሱ ስለመሆኑ ሲናገር ከኤርሚያስ ጋር እጅ ከፍንጅ ተያዙ። ኤርሚያስንም ከአሁን ቀደም እነ ልደቱ ያወጧቸውን ሰነዶች እንደሚያውቅ ያምናል። ልደቱም ደርሷችኋል ይለዋል። (ቪዲዮው ተያይዟል)
እነ ልደቱ እየተመላለሱ የሽግግር መንግስት የሚሉን ኢትዮ 360 የሚያስተጋባላቸው በዋነኛነት የትግሬ ወራሪ ቡድን ከሱዳን ጋር የሚገናኝበት ኮሪደር እንዲሰጠው፣ ወልቃይትና ራያ ከአማራ ተነጥቀው የውጭ ጦር እንዲሰፍርባቸው የተቀመጠውን አላማ ለማሳካት ነው። ሀሳቡ የመነጫው ከእነ ስዬ አብርሃ ነው። እነ ልደቱና ኤርሚያስ ለማስፈፀም እየለፉ ነው። እየሸፋፈኑ የሽግግር መንግስት የሚሉት ይሄን የክህደት ሀሳብ ይዘው ነው። እነ ኤርሚያስ ድርድር ሲሉ የከረሙት ለዚህ እንጅ ለእውነተኛ ድርድር አይደለም። እነ ኤርሚያስ የአሜሪካ ጦር ከገባ ለኢትዮጵያ ሰላም ነው ያሉን ለዚህ አላማቸው ነው። የትግሬ ወራሪ ያሸነፈ ሲመስላቸው ሲደነፉ ከርመው ጋሸና ሲያዝ ከሚዲያ የጠፉት የትግሬ ወራሪን አላማ አስፈፃሚ ስለሆኑ ነው!
አቶ ልደቱ አያሌውን ግን ማመስገን ይገባል! የምናውቀውንም ቢሆን አምኗል። እጅ ከፍንጅ ሲያዝ እንዴት ደስ ይላል።
Via @Getachew Shiferaw
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ።… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
- “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረውየሚነሳው ጉዳዩ ልብ ሰባሪ ነው፣ ያስቃል፣ ያዝናናል፣ ያስገርማል፣ ያሳዝናል፣ ይቀፋል፣ ያሳፍራል፣ ለማመን ያስቸግራል … አንባቢ ስም… Read more: “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረው
- ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!በፖለቲካም ሆነ በአካባቢያዊ አጀንዳ ነፍጥ ያነገቡ እና ጦርነትን አማራጭ አድርገው የሚንቀሳቀሱ ኢ -መደበኛ አደረጃጀቶች ሁሉ የጦር… Read more: ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!